በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለአስተዳደር ሠራተኞች የአስተዳደር ሥልጠና ተሰጠ

December 7, 2019

ኅዳር 16/03/2012 ዓ.ም በካቴድራሉ አስተዳደር ጽ/ቤት ለውጥ /Change management በሚል ርዕስ የአንድ ቀን ሥልጠና ተሰቷል፡፡
ሥልናውን የሰጡት በዚሁ ሙያ ላይ የረጅም ጊዜ አገልግሎት ያላቸው የሰበካ ጉባኤ አባል የሆኑት አቶ ደረጃ ተክሌ ናቸው፡፡

አስተዳደራዊ ለውጥ ቤተ ክርስቴያን ያስፈልጋል፤ ቀደም ሲል የነበሩ የቤተ ክርስቲያን አባቶችና መሪዎች ለሀገሪቱ እና ለቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን በስፋት ያብራሩት አቶ ደረጃ እንደ አባቶቻችን ለሀገራችንና ለቤተ ክርስቲያናችን ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ እና ለሰው ልጅ ሁሉ ስለአንድነት ዘወትር ማስተማር እንደሚገባ፤ አንድነቱም ከራሳችን ነው መጀመር ያለበት እኛ አንድ ሳንሆን ሌላውን አንድ ማድረግ አንችልም፤ የትኛውንም ችግር ያለ አንድነት ሊፈታ አይችልም ብለዋል፡፡

በዘርና በፖለቲክ መለያት አግባብ አይደልም፤ በተለይም በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ሁሉም ሰው የእግዚአብሔር ፍጡር ሆኖ ሳለ በዘርና በፖለቲካ ተለያይቶ ማየት እጅግ ያሳፍራል ብለዋል፡፡
ከቴድራሉ ዓለም አቀፍ እንደመሆኑ መጠን በእስትራቴጂክ ፕላን እና በእቅድ መመራት ይኖርበታል ፤አሰራራችን በሻሻልን እና በለወጥን ቁጥር ካቴድራሉንና የካቴድራሉ ማኅበረ ሰብ እንዲሁም ተገልጋዩን ማኅበረ ላይ ጥሩ ተነሳሽነትን ይፈጥራል ብለዋል፡፡
ካቴድራሉ የቱሪስት መስህብ ቢሆንም ለቱሪስት የተመቻቸ ሁኔታ ባለመኖሩ የሚጠበቅበትን ያህል አይደልም፤ ደረጃውን የጠበቀ ቤተ መጻህፍትም የለውም፤በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶበት ሊሠራ ይገባል ብለዋል፡፡
የካቴድራሉ አስተዳደር ሠራተኞችም በበኩላቸው ሥልጠና አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ይህን መሰል ሥልጠና በየሥራ ዘርፉ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ሃሳባቸውን ገልፀዋል፡፡

የዚህ ዓይነት ሥልጠና ቀደም ሲል በካቴድራሉ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመምህንና ለልዩ ልዩ ሠረተኞች እንደተሰጠ ይታወሳል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/012.jpg 480 640 htc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png htc2019-12-07 08:28:002021-02-25 11:25:15በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለአስተዳደር ሠራተኞች የአስተዳደር ሥልጠና ተሰጠ

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክቡር ቢተወደድ ባሕሩ አብርሐም G+2 የአብነት ት/ቤት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክቡር ቢተወደድ ባሕሩ አብርሐም G+2 የአብነት ት/ቤት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክቡር... Link to: በዓለ አስተርእዮ Link to: በዓለ አስተርእዮ በዓለ አስተርእዮ
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top