በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት

August 25, 2011

ይህ ክፍል ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን፣እንደ አጽዋማት፣ ታላላቅ በዓላት እና የመሳሰሉትን መርሐግብሮች ጊዜውን ጠብቆ ፕሮግራም በማውጣት ሕዝቡን የሚያገለግል ሆኖ በተጨማሪም ልዩ ልዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች ዕለቱንና ሰዓቱን  ጠብቀው እንዲፈጽሙ መዘምራኑን፣ ልዑካኑንና ተጓዳኝ አገልጋዮችን የሚመራና የሚቆጣጠር የመንፈሳዊ አገልግሎት ክፍል ነው፡፡

የቤተክርስቲያኑ ሥዩማን

የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሕዝቡን በሠለጠነ መንገድ ለማገልገል እንዲቻል የሚከተሉት የቤት ክርስቲያን ሥዩማን አሉት፡፡ ሥራቸውም የቤተ እግዚአብሔር አገልግሎት እንዳይታጎል ካህናትን ሠርተው የሚያሠሩ ናቸው፡፡
እነርሱም፡-

  • 1.    ሊቀጠበብት
  • 2.    ቄሰ ገበዝ
  • 3.    ርዕሰ ደብር
  • 4.    ቀኝ ጌታ ፣ግራ ጌታ ፣ አጋፋሪና
  • 5.    ሊቀ ዲያቆናት እየተባለ በየማዕረጋቸው ይጠራሉ፡፡

ከአጋፋሪና ከሊቀ ዲያቆናት በታች ያሉት ደግሞ መጨኔዎች ሲባሉ የሥርዓተ ማሕሌቱን ዕቃዎች በኃላፊነት ከመጠበቅ ሌላ የምርፋቁ ሥርዓት በአግባቡ እንዲከናወን ተግተው ይሠራሉ (ያሠራሉ)፡፡የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በ  365.5 ቀናት (በ13 ወራት)፣ በ4 ሳምንታትና ከሰኞ እስከ እሁድ ባሉት የሳምንት ቀናት በዓመታዊ በዓላት፣ በአጽዋማት፣ እና በመሳሰሉት ካህናቱን፣ ዲያቆናቱን፣ መዘምራኑንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችን በማስተባበር በሰዓታት፣ በማህሌትና በቅዳሴ ሰፊ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ከቅዳሴ መሀል ከቅዳሴ ውጭና በቀኑ የጸሎት ሰዓት በተጓዳኝ ሰፊ የወንጌል ስርጭት በመስጠት የስብከት ሥራን በሰፊው ያካሂዳል፡፡

ይህ መንፈሳዊ አገልግሎት ክፍል በባዕዳን እምነት ወጣቱ እንዳይነጠቅ እና ተተኪ የቤተክርስቲያን ተከታዮችን ለማፍራት እንዲቻል የተለያዩ ኮርሶችን በማዘጋጀት ወጣቶችን በእምነት ያንፃል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png 0 0 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2011-08-25 22:17:592019-07-04 16:02:01የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: አስተዳደራዊ መዋቅር Link to: አስተዳደራዊ መዋቅር አስተዳደራዊ መዋቅር Link to: የልማት እንቅስቃሴዎች Link to: የልማት እንቅስቃሴዎች የልማት እንቅስቃሴዎች
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top