በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

አስተዳደራዊ መዋቅር

August 25, 2011

እንደዘመናዊነቱ ሁሉ አስተዳደሩም በዚሁ እቅድ እንዲመራ የካቴድራሉ አመራር በሚከተለው መልክ ተደራጅቷል፡፡

 

 

    • 1. ሰበካ ጉባዔ፡- ይህ ክፍል ሌሎች ክፍሎችን የሚቆጣጠር ሆኖ የሁሉም ራስ የሆነው የካቴድራሉ ዋና ጽ/ቤት ነው፡፡
    • 2. የቤተክርስቲያን አገልግሎት፡- ይህ ክፍል ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እንደ አጽዋማት፣ ታላላቅ በዓላት እና የመሳሰሉትን ጊዜውን ጠብቆ ፕሮግራም በማውጣት ሕዝቡን የሚያገለግል ሆኖ በተጨማሪም ልዩ ልዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች ሰዓቱን ዕለቱን ጠብቀው እንዲፈጸሙ መዘምራኑን፣ ልዑካኑንና ተጓዳኝ አገልጋዮችን የሚመራና የሚቆጣጠር መንፈሳዊ አገልሎት ክፍል ነው፡፡
    • 3. ንብረት ክፍል፡- ይህ ክፍል በስጦታ የሚገኘውን በፊትም የነበረውን ንብረት የሚጠብቅ፣ ለወደፊትም የገንዘብ ምንጭ የሚገኝበትን መንገድ በሰፊው የሚያጠናና የተገኘውንም ንብረት በአግባቡ የሚጠብቅና የሚቆጣጠር ክፍል ነው፡፡
    • 4. ሙዚየም፡- ይህ ክፍል ጥንታውያን የሆኑ ንዋያተ ቅድሳትን፣ አልባሳትን፣ መጻሕፍትንና የመሳሰሉትን የሚጠብቅ ሌሎችንም ጥንታውያን የሆኑ ዕቃዎችን እየገዛ የሚያጠራቅም ለጐብኝዎችም ሰዓቱን፣ ዕለቱን ለይቶ የሚያሳውቅና የሚያስጐበኝ ክፍል ነው፡፡ ካቴድራሉ በዚህ ክፍል ውስጥ የተለያዩ የመስቀል ዓይነቶችን ያሳተማቸውን አያሌ መጻህፍትንና በስጦታ የተገኙ ንዋያተ ቅድሳትን አስቀምጦ ለአያሌ ጐብኝዎች በማስጐብኘት ላይ ይገኛል፡፡
    • 5. ቁጥጥር ክፍል ፡- ይህ ክፍል ካቴድራሉ እንደ ዕድገት ደረጃው ቀስ በቀስ ያቋቋማቸው አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ቁጥጥር ክፍል ይህ ክፍል ከተለያዩ አቅጣጫ የተሰበሰበ ገንዘብና ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳት በአግባቡ ተመዝግቦ ገቢና ወጪ መሆኑን የሚከታተል ክፍል ነው፡፡
    • 6. ሒሳብ ክፍል፡- ይህ ክፍል በልዩ ልዩ መንገድ የተሰበሰበውን ገንዘብ በዘመናዊ ቀመር አስልቶና መዝግቦ ያመቱን ገቢና ወጪ ለይቶ በማሳየት የሒሳብ ሥራው ሥርዓት ባለው መንገድ እንዲከናወን የሚያደርግ ሲሆን ለሰራተኞች በየወሩ የደመወዛቸውን መጠን እያሰላ እንዲከፈላቸው ለገንዘብ ቤት የሚያስተላልፍ ክፍል ነው፡፡
    • 7. ገንዘብ ቤት፡- ይህ ክፍል ከልዩ ልዩ ገቢዎች የተገኘውን ገንዘብ ከሒሳብ ክፍል በሚሰጠው ሰነድ መሠረት አገናዝቦ ገንዘቡን ባንክ በማስገባት የሚጠብቅና የሠራተኛ ደመወዝን የሚከፍል ክፍል ነው፡፡
    • 8. ሕግ ክፍል፡- ይህ ክፍል ካቴድራሉ ሕጋዊ ሰውነት ያለው ክፍል በመሆኑ የመከሰስም ሆነ የመክሰስ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ ካቴድራሉን ወክሎ ሕጋዊ ሥራዎችን የሚያከናውን ክፍል ነው፡፡
    • 9. ምግባረ ሠናይ ክፍል፡-ይህ ክፍል የተለያዩ በጎ አድራጊ ግለሰዎችንና ድርጅቶችን ኢያስተባበረ ችግረኞችን የሚረዳ ክፍል ነው፡፡
    • 10. የቱሪስት አስጐብኚ ክፍል፡- ይህ ክፍል የተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ጐብኚዎችን በመቀበልና ካቴድራሉ ያሉትን ቅርሳቅርሶች በማስረዳት የማስተናገድ ሥራን ያከናውናል፡፡
    • 11. የተክሊል እና የክርስትና ክፍል፡- ይህ ክፍል በሥርዓተ ተክሊልና ቅዱስ ቁርባን ጋብቻቸውን ለመፈፀም የሚመጡትን ተጋቢዎች፣ እንዲሁም ጥምቀተ ክርስትናን ለመቀበል የሚመጡትን ምዕመናን ተቀብሎ የሚያስተናግድና ማስረጃ አዘጋጅቶ የሚሰጥ ክፍል ነው፡፡
    • 12. መዝብ ቤትና እስታስቲክስም ይገኙበታል፡፡

 

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png 0 0 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2011-08-25 22:15:282019-07-04 16:02:01አስተዳደራዊ መዋቅር

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: ቅ/ሥ/ካቴድራል Link to: ቅ/ሥ/ካቴድራል ቅ/ሥ/ካቴድራል Link to: የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት Link to: የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top