በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

የልማት እንቅስቃሴዎች

August 25, 2011

ካቴድራሉ በልማት በኩል የተከተለው አቅጣጫ

የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በሁሉም አቅጣጫ መሪ እንደመሆኑ መጠንና አስተዳደራዊ ይዘቱም ሰፊ በመሆኑ ገቢው ያኑ ያህል በቂ መሆን ስለሚገባው ከመንግሥት ከተሰጠው ጋሻ መሬት በተጨማሪ ት/ቤት፣ የሙካሽ ሥራ፣ የሥጋጃ ሥራ፣ የአልባሳት ማዘጋጃ፣ የመጻህፍት ማዘጋጃ እና በነዚህ ክፍሎች የተዘጋጁትን የምርት ውጤቶች ለሕዝብ በማቅረብ የሚከፋፈሉባቸው ሱቆች ከአዲስ አበባ እስከ ክ/ሀገር አቋቁሞ ነበር፡፡

ከነዚህ በተጨማሪ ዘመኑ እየሰለጠነ በሄደ መጠን ካቴድራሉ ከህብረተሰቡ የዕድገት ደረጃ ጋር አብሮ እንዲራመድ ከአካባቢው በጣም ዘመናዊና ጠንካራ የሆኑ ሕንፃዎችን አስገንብቶ ከኪራይ በሚያገኘው ገቢ አስተዳደራዊ ዘርፉን ለማስፋፋት ችሎ ነበር፡፡ ፍልውሃ ያለውን ዘመናዊ ሆቴል የራሱ በማድረግ ከቅድስት ሥላሴ ማየ ሕይወትና ከሆቴሉ ከፍ ያለ ገቢ ያገኝ ነበር፡፡ይህ ሁሉ ገቢ በ1966 ዓ.ም. በተደረገው የመንግሥት ለውጥ ካቴድራሉ በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍል እንደደረሰው ሁሉ ሀብቱ ሲወረስ ብዙ ገቢ የሚያስገኝለት ት/ቤትም ደረጃው ከ12ኛ ወደ 8ኛ ክፍል ዝቅ እንዲል በመደረጉ የነበረው ፈጣን እንቅስቃሴ ተገታ፡፡
የካቴድራሉ አስተዳደር ጊዜውን ተከትሎ በዘዴ እየተራመደ ት/ቤቱን በወቅቱ አስተዳዳሪ በነበሩት ሊቀሥልጣናት አባ ሀብተ ሥላሴ (ዶ/ር በአቡነ ጢሞቴዎስ) ጥረት ሳይወሰዱ በቀሩት ቦታዎች ምእመናኑን በማደራጀት ሥራው ሳይቋረጥ ሲያዘግም ቆይቶ ቀስ በቀስ የካቴድራሉን ገቢ ሊያዳብሩ የሚችሉ ቋሚ ተግባራትን ሲያከናውኑ እንደነበር ይነገራል፡፡

  • 1.    ሁለገብ አዳራሽ

ይህ አዳራሽ በሊቀ ሥልጣናት አባ ገብረ ማርያም አጽብሐ የተሠራ ሲሆን እጅግ ዘመናዊ እቅድን ተከትሎ የተሠራ ሆኖ ለሠርግ፣ ለስብሰባ፣ ለሙት ዓመት፣ መታሰቢያና ለመሳሰሉት አገልግሎቶች፣ ለአገልጋዮች በነፃ አገልግሎት ሲሰጥ ለውጭ ሰዎች ደግሞ በገንዘብ ይከራያል፡፡ ከአዳራሹ ጋር ተያይዞ የተሠራው የፉካ መቃብርም ለ7 ዓመታት ውል እየተከራየ የካቴድራሉን ገቢ በማሳደግ ላይ ከመሆኑም ሌላ አብሮ የተገነባው ፎቅም ለልዩ ልዩ ድርጅቶች ተከራይቶ ቋሚ ገቢ በማስገኘት ላይ ነው፡፡

  • 2.    ከፍተኛ ክሊኒክ

ይህ ሕንፃ በአንዲት የተከበሩ የቤተክርስቲያን ልጅ ከሆኑት ከወ/ሮ እስከዳር ገ/ሕይወት አስተዋጽኦ ጭምር የተገነባ ዘመናዊ ክሊኒክ ሲሆን ሥራው ተጠናቆና ተመርቆ ካቴድራሉ ለባለሙያዎች አከራይቶት ሥራውን እያካሄደ ይገኛል፡፡

  • 3. ት/ቤት

ሥላሴ ት/ቤት በአንዲት ክፍል በ1955 ዓ.ም. ለካህናት ማሰልጠኛ ተብሎ በማታው ትምህርት ክፍል የተጀመረው ት/ቤት አድጎና ተስፋፍቶ ከላይ እንደተገለጸው ተቋርጦ የነበረው  የ2ኛ ደረጃ ትምህርት በወቅቱ የካቴድራሉ አስተዳዳሪ በነበሩት ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገወይን ገብረ ሥላሴ /አቡነ ሠላማ/ አስተባባሪነት በማኅበረ ካህናትና በመላው ሠራተኛ ጥረት እጅግ ባማረ እና በተዋበ የተገነባው ሕንፃ ጥቅምት 2ዐ ቀን 1997 ዓ.ም. ተመርቆ ሥራ ላይ ውሏል፡፡ ይህም የሚያሳየው ካቴድራሉ ርእሰ አድባራትና ገዳማት እንደመሆኑ መጠን ሌሎች አብያተክርስቲያናት ፈለጉን ተከትለው ብዙ ሥራዎችን እያከናወኑ በመሆናቸው አሁንም የመሪነቱን ሥፍራ አለመልቀቁን ያሳያል፡፡ ካቴድራሉ በነባሩ ት/ቤት ባለው ሰፊ ቦታ በቅርብ ጊዜ ዘመናዊ ሕንፃ ገንብቶ ኮሌጅ ለመክፍት እቅድ ይዟል፡፡ ይህ ኮሌጅ ሲከፈትም ካቴደራሉ በሁለገብ መልኩ ተጠቃሚ ከመሆኑም ሌላ በውስጡ ያሉ ካህናት፣ መምህራንና ሠራተኞች እውቀታቸውን ይበልጥ እንደሚያሳድጉበት ይጠበቃል፡፡

  • 4. በአሁኑ ወቅትም  በ22 ማዞሪያ ባለ 4 ፎቅ ህንፃ በመሠራት ላይ ይገኛል.
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png 0 0 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2011-08-25 22:18:452019-07-04 16:02:01የልማት እንቅስቃሴዎች

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት Link to: የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት Link to: የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር (ሙዚየም) Link to: የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር (ሙዚየም) የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር (ሙዚየም...
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top