አስተዳደራዊ መዋቅር

እንደዘመናዊነቱ ሁሉ አስተዳደሩም በዚሁ እቅድ እንዲመራ የካቴድራሉ አመራር በሚከተለው መልክ ተደራጅቷል፡፡

 

 

    • 1. ሰበካ ጉባዔ፡- ይህ ክፍል ሌሎች ክፍሎችን የሚቆጣጠር ሆኖ የሁሉም ራስ የሆነው የካቴድራሉ ዋና ጽ/ቤት ነው፡፡
    • 2. የቤተክርስቲያን አገልግሎት፡- ይህ ክፍል ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እንደ አጽዋማት፣ ታላላቅ በዓላት እና የመሳሰሉትን ጊዜውን ጠብቆ ፕሮግራም በማውጣት ሕዝቡን የሚያገለግል ሆኖ በተጨማሪም ልዩ ልዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች ሰዓቱን ዕለቱን ጠብቀው እንዲፈጸሙ መዘምራኑን፣ ልዑካኑንና ተጓዳኝ አገልጋዮችን የሚመራና የሚቆጣጠር መንፈሳዊ አገልሎት ክፍል ነው፡፡
    • 3. ንብረት ክፍል፡- ይህ ክፍል በስጦታ የሚገኘውን በፊትም የነበረውን ንብረት የሚጠብቅ፣ ለወደፊትም የገንዘብ ምንጭ የሚገኝበትን መንገድ በሰፊው የሚያጠናና የተገኘውንም ንብረት በአግባቡ የሚጠብቅና የሚቆጣጠር ክፍል ነው፡፡
    • 4. ሙዚየም፡- ይህ ክፍል ጥንታውያን የሆኑ ንዋያተ ቅድሳትን፣ አልባሳትን፣ መጻሕፍትንና የመሳሰሉትን የሚጠብቅ ሌሎችንም ጥንታውያን የሆኑ ዕቃዎችን እየገዛ የሚያጠራቅም ለጐብኝዎችም ሰዓቱን፣ ዕለቱን ለይቶ የሚያሳውቅና የሚያስጐበኝ ክፍል ነው፡፡ ካቴድራሉ በዚህ ክፍል ውስጥ የተለያዩ የመስቀል ዓይነቶችን ያሳተማቸውን አያሌ መጻህፍትንና በስጦታ የተገኙ ንዋያተ ቅድሳትን አስቀምጦ ለአያሌ ጐብኝዎች በማስጐብኘት ላይ ይገኛል፡፡
    • 5. ቁጥጥር ክፍል ፡- ይህ ክፍል ካቴድራሉ እንደ ዕድገት ደረጃው ቀስ በቀስ ያቋቋማቸው አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ቁጥጥር ክፍል ይህ ክፍል ከተለያዩ አቅጣጫ የተሰበሰበ ገንዘብና ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳት በአግባቡ ተመዝግቦ ገቢና ወጪ መሆኑን የሚከታተል ክፍል ነው፡፡
    • 6. ሒሳብ ክፍል፡- ይህ ክፍል በልዩ ልዩ መንገድ የተሰበሰበውን ገንዘብ በዘመናዊ ቀመር አስልቶና መዝግቦ ያመቱን ገቢና ወጪ ለይቶ በማሳየት የሒሳብ ሥራው ሥርዓት ባለው መንገድ እንዲከናወን የሚያደርግ ሲሆን ለሰራተኞች በየወሩ የደመወዛቸውን መጠን እያሰላ እንዲከፈላቸው ለገንዘብ ቤት የሚያስተላልፍ ክፍል ነው፡፡
    • 7. ገንዘብ ቤት፡- ይህ ክፍል ከልዩ ልዩ ገቢዎች የተገኘውን ገንዘብ ከሒሳብ ክፍል በሚሰጠው ሰነድ መሠረት አገናዝቦ ገንዘቡን ባንክ በማስገባት የሚጠብቅና የሠራተኛ ደመወዝን የሚከፍል ክፍል ነው፡፡
    • 8. ሕግ ክፍል፡- ይህ ክፍል ካቴድራሉ ሕጋዊ ሰውነት ያለው ክፍል በመሆኑ የመከሰስም ሆነ የመክሰስ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ ካቴድራሉን ወክሎ ሕጋዊ ሥራዎችን የሚያከናውን ክፍል ነው፡፡
    • 9. ምግባረ ሠናይ ክፍል፡-ይህ ክፍል የተለያዩ በጎ አድራጊ ግለሰዎችንና ድርጅቶችን ኢያስተባበረ ችግረኞችን የሚረዳ ክፍል ነው፡፡
    • 10. የቱሪስት አስጐብኚ ክፍል፡- ይህ ክፍል የተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ጐብኚዎችን በመቀበልና ካቴድራሉ ያሉትን ቅርሳቅርሶች በማስረዳት የማስተናገድ ሥራን ያከናውናል፡፡
    • 11. የተክሊል እና የክርስትና ክፍል፡- ይህ ክፍል በሥርዓተ ተክሊልና ቅዱስ ቁርባን ጋብቻቸውን ለመፈፀም የሚመጡትን ተጋቢዎች፣ እንዲሁም ጥምቀተ ክርስትናን ለመቀበል የሚመጡትን ምዕመናን ተቀብሎ የሚያስተናግድና ማስረጃ አዘጋጅቶ የሚሰጥ ክፍል ነው፡፡
    • 12. መዝብ ቤትና እስታስቲክስም ይገኙበታል፡፡