ሰንበት ትምህርት ቤት

ሰ/ት/ቤት በዘመነ ብሉይ

የሰንበት ት/ቤት ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ የነበረው ነው፡፡ ለምሳሌ በዘዳግም “እነዚህ ቃሎች በልባችሁና በነፍሳችሁ አኑሩ እነርሱንም ለምልክት በእጃችሁ ላይ እሰሩአቸው በአይኖቻችሁም መካከል እንደክታብ ይሁን ልጆቻችሁንም አስተምሩአቸው በቤትህም ስትቀመጥ በመንገድህም ስትሄድ ስትነሳም አጫውታቸው” የሚል እናነባለን (ዘዳ 1÷6-9)
ከዚህ በላይ እንደተጠቀሰው እስራኤላውያን ልጆቻቸውን ሕገ እግዚአብሔር እንዲያስተምሩአቸው ታዘዋል በትእዛዙም መሰረት ሕፃናቶቻቸውን በቤተ እግዚአብሔርና በቤታቸው ሕገ ኦሪትን እያስተማሩ ያሳድገôቸው እንደነበር ለማወቅ እንችላለን፡፡

ሰ/ት/ቤት በዘመነ ሐዲስ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባስተማረበት ዘመንም ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው በመንግስተ ሰማያት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ነው; ባሉት ጊዜ አንድ ሕፃን ጠርቶ በመካከላቸው አቆመ /እውነት እውነት እላችኋለሁ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ ወደ መንግስተ ሰማያት ከቶ አትገቡም/ ብሎ ሕፃናትን ለቤቱ ስራ ምሳሌ አድርጎ እንዳቀረባቸው እንረዳለን፡፡ ስለ ትሕትናም ለማስተማር በፈለገ ጊዜ አንድ ሕፃን ጠርቶ /ሰው ለክብር ቢወድ ከሁሉ በኋላ የሁሉም አገልጋይ ይሁን/ ካለ በኋላ እንደዚህ ካሉ ሕፃናት አንዱ/ በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል/ በማለት ሕፃናት ለሁሉም ምሳሌ እንደሆኑ ተናግሯል፡፡ / ማቴ 17÷ 2-4 ፣ ማር 9÷35-36፣ ሉቃስ 9÷46-47/

በሌላውም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሕፃናትን ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲመጡ አይተው ይገስጻôቸው ጀመር እርሱ ግን ሕጻናትን ተዋቸው ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክላôቸው መንግሥተ ሰማያት እንደ እነርሱ ላሉት ናትና / በማለት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የሚገባቸው መሆኑን አስገንዝባôቸዋል /ማቴ 19 ፥14/
በመሆኑም ሰ/ት/ቤት በዘመነ ሐዲስ በ 200 ዓ.ም. በፈረንሳይ ሀገር በፓሪስ ከተማ ተጀምሯል ከዚያም በኋላ አውሮፓ እንደተስፋፋ እና በሌሎች አህጉራትም እንደተቀôቀôመ ተረጋግጧል፡፡
ይህንን መሰረት በማድረግ ቤተክርስቲያናችን ሕገ ወንጌልን ለማስፋፋት ከሚያስፈልገôት ዋና ዋና ነገሮች አንዱ የሰ/ት/ቤትን ማቀôቀôምና ማደራጀት መሆኑን ተገንዝባ ሰ/ት/ቤትን በየአጥቢያ ቤተክርስቲያን በስፋትና በጥልቀት እንዲቀôቀôም አድርጋለች፡፡

በአገራችን በኢትዮጵያም በዘመናዊ መልክ እንደ አሁኑ ባይቀôቀôምም እንካô ከሁሉ በፊት እንደ ነበር የታመነ ነው፡፡ ይኽውም በኢትዮጵያ ሊቃውንት ወይም መምህራን በየቤተክርስቲያኑ በየደጀ ሰላሙና በየዛፉ ስር በየመንደሩም ጭምር ሕጻናትን በመሰብሰብ ያስተምሩት የነበረው የሰንበት ትምህርት ቤት መሰረትና መነሻ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

ሰ/ት/ቤት በአገራችን በዘመናዊ መልክ በመንበረ ጸባዖት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል መቋቋም

ለሰ/ት/ቤት መጀመርና መስፋፋት የመጀመሪያ የሚሆነው ይህው ታላቅ ካቴድራል ሲሆን ካቴድራሉ ከመቆርቆሩ ቀደም ብሎ በዳግማዊ ምኒሊክ በ 1883 ዓ.ም መካነ ሥላሴ የዛሬው በ®ለ ወልድ እየተባለ የሚጠራው ቤተክርስቲያን ተተክሎ ለ41 ዓመታት እየተገለገለበት ከቆየ በኋላ ለአዲሱ ካቴድራል ምስረታ በ1924 ዓ.ም. የመሰረት ድንጋይ ተጥሎ በታኅሳስ 30 ቀን 1936 ዓ.ም. ተፈጽሞ በይፋ መካነ ሥላሴ የነበረው በ®ለ ወልድ ተብሎ አዲሱ ቤተክርስቲያን ደግሞ መ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል በሚል ስያሜ ተመርቆ ዓለም አቀፋዊ አገልግሎቱን የጀመረ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ለዚህ ታላቅ የምርቃት ሥነ-ስርዓት ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ከተለያዩ አገራት የጠሯቸውን የውጭ አገር እንግዶች፣ የአገር ውስጥ ባለስልጣናት እና ሰፊውን ሕዝብ በአግባቡ ለማገልገል ይቻል ዘንድ የወንድ ወጣቶች እገዛ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል፡፡ በመሆኑም የተለያዩ ወጣቶች ተሰብስበው ስለ ዕለቱ የመስተንግዶ ሥራና ሊኖር የሚገባውን የሥነ-ምግባር ሥርዓተ-ትምህርት ከተሰጣቸው በኋላ በምርቃቱ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ የተጣለባቸውን አደራ ተወጥተዋል፡፡ እንግዶቹና ምዕመናኑ በታላቅ አክብሮት ለንጉሠ ነገሥቱ ምስጋና በማቅረባቸውና የወጣቶቹ የመስተንግዶ አገልግሎት ቀጣይነት እንዲኖረው ፈቃድ በመስጠቱ የካቴድራሉ አስተዳደርም ለወጣቶቹ መምህር በመመደብ ትምህርቱን ቀጠለ፡፡
በመሆኑም በዚሁ ዓመት ማለትም በ1936 ዓ.ም. በወቅቱ የካቴድራሉ የመጀመሪያው መምህር /አስተዳዳሪ/ ሆነው በተሾሙት በሊቀ ሥልጣናት በአባ መልዕክቱ / በኋላም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የኢትዮጵያ ፓትርያሪክ ተብለው በተሾሙት/ አገልግሎቱ ቀጣይነት እንዲኖረው እንደተቋቋመ ለመረዳት የተቻለ ሲሆን በኋላም ከሦስት አመት በኋላ በ1939 ዓ.ም. በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም አሁን ተምሮ ማስተማር እየተባለ በሚጠራው ማህበር ተጠናክሮ ተቀôቀôመ፡፡

ወጣቶቹ በሚያገኙት ትምህርት በየሳምንቱ ዕውቀት እያገኙ በመምጣታቸውና ለቅዳሴ የሚመጡትን ምዕመናንንና እንግዶችን በተገቢው መንገድ ከማስተናገድም በተጨማሪ የነገሥታቱንና የመኳንንቱን ልጆች በቅዳሴ ሥነ-ስርዓት እንዳያውኩ በአዳራሽ እያስተማሩ የቀጠሉ ሲሆን የወጣቶቹም እንቅስቃሴ እየተጠናከረ በመምጣቱ ለካቴድራሉ አገልግሎት ትልቅ ደረጃ መድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
ጉዞው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረና እየተስፋፋ ለመምጣቱ ዋናውና ጉልህ ያደረገው ንጉሠ ነገሥቱና ሹማምንቱ በወጣቶቹ አገልግሎት በመደሰታቸውና ትኩረትም በመስጠታቸው ሲሆን ከዚሁም ጎን ለጎን በወቅቱ በቦታው ሲመሩና ሲያገለግሉ የነበሩ ሊቃውንትና ካህናት ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት መሆኑን ታሪክ ያስረዳናል፡፡
ቀስ በቀስም የሰ/ት/ቤት አገልግሎት በመላ አገሪቱ አድማሱን እያሰፋ በመምጣቱ በቤተክርስቲያን አገልግሎትም አዲስ ምዕራፍ መክፈቱ ከዕለት ወደ ዕለት ይፋ እየሆነ መጣ፡፡ በመቀጠልም የሰ/ት/ቤት አገልግሎት በወንዶች ብቻ ተወስኖ እንዳይቀር ማህበረ ክርስቶስ የሴት ልጅ እድገት በሃይማኖት የደናግል ሴቶች ማህበር በሚል ስም የሴቶች እንቅስቃሴ እንደተጀመረ የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል የ 10 ዓመት የስራ ውጤት በሚል በተዘጋጀው መጽሐፍ ላይ የሚገልጸውን በአጭሩ እንመልከት፡፡

ሴቶች ልጆች በዘመናዊ ትምህርት ከወንዶች ጎን ተሰልፈው እኩል መማር የጀመሩበት ጊዜ ረጅም ባይሆንም በተለይ በቤተ ክርስቲያን በኩል ሁሉ ነገር በወንዶች ብቻ ተወስኖ መቆየቱ ግልጽ ነው፡፡ የሴቶች ከቤተክርስቲያን አገልግሎት መራቅ ምክንያት በማድረግ ማኅበረ ክርስቶስ ሰኔ 1/1956 ዓ.ም. ከ 20 በማይበልጡ በዳግማዊ ሚኒሊክ ትምህርት ቤት ወጣት ሴት ተማሪዎች በተለይም በእህት አፀደክርስቶስ ተፈራ አሰባሳቢነት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ስር ለመሰባሰብ ቻሉ፡፡ በዚያን ጊዜ እንደዚህ አይነቱ ማኀበር በአገራችን ውስጥ የመጀመሪያ ስለነበር በሕዝቡ ዘንድ ብዙ ትችትና መገረምን አስከትሎ ነበር፡፡ ቢሆንም ሰው ካሰበው እግዚአብሔር የፈቀደው ይበልጣልና በአምላክ ቸርነት በአንዳንድ ሰዎች አበረታችነትና ደጋፊነት እንዲሁም በልጆቹ መንፈሰ ጠንካራነት ማኀበሩ ሥራውን ቀጠለ፡፡

ማኀበሩ ስሙ እንደሚያመለክተው በክርስቶስ የተመሰረተ ስለሆነ ዓላማው ክርስቲያናዊ ትምህርትን ተምሮ ማስተማር’ ሰብዓዊ ርኀራኄና በክርስቲያናዊ ትምህርት መሰረት መፈጸም’ ክርስቲያናዊና ብሔራዊ ባህልን ለመጠበቅና ለማስከበር እንዲሁም ሴት ልጅ በማህበራዊ ኑሮ በቤተክርስቲያንና በቤተሰብ በሚገባ አገልግሎትን መስጠት እንድትችል ለማድረግ ነው፡፡ በሚል ይህ ለህትመት የበቃው መጽሐፍ አስነብቧል፡፡
በዚህ መልክ የተጀመረው የሴቶች የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት በቤተክርስቲያን ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የቅዳሴ ተሰጥዎን ለመቀበል የበቁት የዚሁ ማኀበር አባላት መሆናቸውን ማንም የማይዘነጋው ሲሆን ከዚህም በላይ የተለያዩ መዝሙሮችን በማጥናት ከቅዳሴ ሥነ-ስርዓት በኋላና በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ጊዜ የደንብ ልብስ ለብሶ በመዘመር ለቤተክርስቲያን ድምቀት ሰጥተዋታል፡፡ በተለይም ቅድስት ቤተክርስቲያን ሴትና ወንድ ብላ ሳታበላልጥ ለሴት ልጆች እውቀት መሻሻልና የጾታ ልዩነት እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥረት አድርጋለች ከነዚህም መካከል ድምጸ ተዋህዶ እየተባለ በሚወጣው ወርሐዊ ጋዜጣ ላይ የሴቶች አምድ በሚል ርዕስ የሴት ልጅን እኩልነት ለማስተማር ቀዳሚ መሆኗንም ታሪክ ያስረዳል፡፡

ከዚህ ቀደም ብሎ በካቴድራሉ ከ1936 ዓ.ም. ከሰንበት ት/ቤቱ አመሰራረት ጀምሮ የነበረና በሐዋርያዊ ድርጅት ስር በካቴድራሉ የበላይ ጠባቂነት ይመራ የነበረ ማህበረ እስጢፋኖስ ግብረ ልዑካን የመነኮሳትና የዲያቆናት እንዲሁም የወጣቶች ማህበር በሚል ስያሜ የተቋቋመ ማህበር ነበር፡፡ ይህ ማህበር የአዲስ አበባ አድባራት ካህናትን አጠቃሎ በመያዝ የሚሰራ ሲሆን ካቴድራሉ ሁሉንም እንደየ ችሎታውና ፍላጎቱ በማደራጀት መንፈሳዊ አገልግሎቱ ዘመናዊና የተሟላ እንዲሆን አስችሎታል፡፡ ማኅበሩ ወጣቶችን ያቀፈ እንደ መሆኑ መጠን በቅንጅት መልካም ስራዎችን በመስራት ላይ እያለ በገጠመው የውስጥ ችግር ምክንያት ብዙ ፈተና አሳልፎ በመጨረሻም በወቅቱ በነበሩት የካቴድራሉ አስተዳዳሪና በሚመለከታቸው ሰዎች ብርቱ ጥረት በድጋሚ የወንድ ወጣቶቹን እንቅስቃሴ በማጠናከርና እንዲንሰራራ በማድረግ እንዲሁም የደንብ ልብስ /ዩኒፎርም/ በማሰፋት ማህበረ ሥላሴ በሚል መጠሪያ በድጋሚ እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡ ይህ በአዲስ መልክ የተደራጀው ማኅበር ውስጣዊ አቅሙን እያጠናከረና እየሰፋ ከመምጣቱም ባሻገር በሌሎች አድባራት እየሄዱ ልምድ በማካፈል ለሌሎች ወጣቶች መንፈሳዊ ቅናትን በማሳደር ቀስ በቀስ በሁሉ ቦታ እንዲስፋፋ በማድረግ ከፍተኛ ለውጥ አመጡ፡፡ ማህበሩም እስከ 1968 ዓ.ም. ድረስ በዚሁ መጠሪያ ስም ይጠራ ነበር፡፡
ከላይ በአጭሩ የተገለጸው የሰ/ት/ቤት እንቅስቃሴ እጅግ በጥልቅና ሰፋ ባለ መልኩ በተለይ ንጉሠ ነገሥቱ በሥልጣን እስከነበሩበት ጊዜ ድረስ በየዓመቱ የ4 እና የ6 ወር እንዲሁም የዓመት ትምህርት ያገኙ ተማሪዎች ከንጉሠ ነገሥቱ የሠርተፊኬትና የተለያዩ ሽልማትን በማግኘት በውጭ ሃገር ጭምር በመሄድ ተሳትፎአቸውን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ታሪክ ይነግረናል፡፡

በመቀጠልም እንቅስቃሴውን እስከ 1966 ዓ.ም እያስፋፋ ከቆየ በኋላ በወታደራዊው ደርግ ዘመነ መንግስት ቀደም ሲል ከ1966 ዓ.ም በፊት የነበረው እውቅና ቀርቶ በቤተክርስቲያን ብቻ ተወስኗል፡፡ በመሆኑም በወንዶች ማህበረ ሥላሴ በሴቶች ማህበረ ክርስቶስ በሚል መጠሪያ ይታወቁ የነበሩት ሁለቱ ማህበራት በወቅቱ የካቴድራሉ አስተዳዳሪ የነበሩት ሊቀ ሥልጣናት ዶ/ር አባ ሀ/ሥላሴ ተስፋ / በኋላም አቡነ ጢሞቴዎስ/ ለአመራርና ለቁጥጥር እንዲያመች ሁለቱ ማኅበራት በአንድነት ተዋህደው መመራት አለባቸው ስላሉ አባላቱም ጉዳዩ ስላስደሰታቸው በ1969 ዓ.ም. በአንድነት ተዋህደው የማኅበሩ መጠሪያ ስም ማኅበረ ክርስቶስ ዘመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል፡፡ ተብሎ ተሰየመ፡፡

መኅበሩም ማኅበረ ክርስቶስ በሚል መጠሪያ አገልግሎቱን በመቀጠል ላይ ሳለ በስንዴ መካከል እንክርዳድ አይጠፋምና መናፍቃን በታላቁና ለሰ/ት/ቤቶች መሰረት በሆነው የወጣት ማኀበር በመግባታቸው ውስጥ ውስጡን ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ነገሮችን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥረው አላማቸውን ከግብ ከማድረሳቸው በፊት በፈቃደ እግዚአብሔርና በወቅቱ የካቴድራሉ አስተዳዳሪ በነበሩ በሊቀ ሥልጣናት አባ ተክለሚካኤል አባይ /በኋላም አቡነ ሚካኤል/ እንዲሁም በካቴድራሉ ሰራተኞችና አስተዳደር ስለተደረሰባቸው ቤቱን ጥለው እንዲወጡ ተደርጓል፡፡ በመሆኑም ማኅበረ ክርስቶስ ዘመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል፡፡ ተብሎ ይጠራ የነበረውን የወጣቶች ማኅበር በድጋሚ በአዲስ መንፈስ እንቅስቃሴውን ይቀጥል ዘንድ በወቅቱ በነበሩት በእኚህ አባት ትኩረት ስለተሰጠው ስሙ ተቀይሮ የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት መባል አለበት በሚል ማሳሰቢያ የሰጡ ሲሆን ይህም ተቀባይነት አግኝቶ በዚሁ መጠሪያ እንዲጠራ ሆኗል፡፡

ከዚህ በኋላ የሰ/ት/ቤቱ የተለያዩ ንብረቶች በተለያየ መንገድ የተበታተኑ ሲሆን በመጨረሻም ጥቂት በሆኑ ወጣቶች እንደገና ለማጠናከር ተሞክሮ ለውጥ ማሳየት ባለመቻሉ እንደገና በካቴድራሉ አስተዳደር ቀና ድጋፍና በወቅቱ የሰ/ት/ቤቱ ያሬዳዊ ዜማና የመጽሐፍ ቅዱስ መምህር በነበሩት በመምህር ኤልያስ አብርሃ / በኋላም ንቡረዕድ ሆነው በተሾሙና የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ በሆኑት/ ብርቱ ጥረት በድጋሚ እንዲቋቋም ተደርጎ በአሁኑ ሰዓት ያለምንም ችግር በ12 ዓመት 4 አመራር ሂደት አጠናቆ አሁን በ 5ኛ አመራር በጥሩ ሁኔታ እንቅስቃሴ እየሰጠ ይገኛል፡፡