አገልግሎቶች

  • ሁለገብ አዳራሽ

ይህ አዳራሽ በሊቀ ሥልጣናት አባ ገብረ ማርያም አጽብሐ የተሠራ ሲሆን እጅግ ዘመናዊ እቅድን ተከትሎ የተሠራ ሆኖ ለሠርግ፣ ለስብሰባ፣ ለሙት ዓመት፣ መታሰቢያና ለመሳሰሉት አገልግሎቶች፣ ለአገልጋዮች በነፃ አገልግሎት ሲሰጥ ለውጭ ሰዎች ደግሞ በገንዘብ ይከራያል፡፡ ከአዳራሹ ጋር ተያይዞ የተሠራው የፉካ መቃብርም ለ7 ዓመታት ውል እየተከራየ የካቴድራሉን ገቢ በማሳደግ ላይ ከመሆኑም ሌላ አብሮ የተገነባው ፎቅም ለልዩ ልዩ ድርጅቶች ተከራይቶ ቋሚ ገቢ በማስገኘት ላይ ነው፡፡

  • ከፍተኛ ክሊኒክ

ይህ ሕንፃ በአንዲት የተከበሩ የቤተክርስቲያን ልጅ ከሆኑት ከወ/ሮ እስከዳር ገ/ሕይወት አስተዋጽኦ ጭምር የተገነባ ዘመናዊ ክሊኒክ ሲሆን ሥራው ተጠናቆና ተመርቆ ካቴድራሉ ለባለሙያዎች አከራይቶት ሥራውን እያካሄደ ይገኛል፡፡

  • ዘመናዊ ት/ቤት

የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ት/ቤት በሦስት የትምህርት ዕርከኖች ወይም ደረጃዎች ተደራጅቶ በርካታ ወጣቶችን እያስተማረ ይገኛል፡፡ እነዚህም

  • 1.    አፀደ ህፃናት
  • 2.    የ1ኛ ደጃ ት/ቤት
  • 3.    የ2ኛ ደረጃ እና መሰናዶ ት/ቤቶች ናቸው፡፡

በ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎችን እንደገና ማስተናገድ የጀመረው በ1ኛ ደረጃው ት/ቤት በ1996 ዓ.ም 9ኛ ክፍል በመክፈት ነበር፡፡
በ1997 ዓ.ም. አዲስ ያሰራውን ህንፃ ለ2ኛ ደረጃና ኮሌጅ መሰናዶ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተናገደ ይገኛል፡፡

 

  • የተለያዩ ካፌዎችና መኖሪያ ቤቶቾ
  • በአሁኑ ወቅትም  በ22 ማዞሪያ ባለ 4 ፎቅ ህንፃ በመሠራት ላይ ይገኛል