የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል 2ኛና መሰናዶ ት/ቤት ድርጅታዊ አቋም

የቦታው ሁኔታ

  • በአራዳ ክ/ከተማ አራት ኪሎ ከፓርላማ አጠገብ ወይም ከወ.ወ.ክ.ማ. ጀርባ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን፣
  • ወጣ ገባ የሌለው ግቢው በአስፋልት የተነጠፈ ለትምህርት ሥራ ምቹነት ያለው ከማንኛውም የፀጥታ ችግር የተከለለ፣
  • ፀጥታንና ጤናን ከሚያውኩ ችግሮች፣
  • የውሃ፣ የመብራት፣ የትራንስፖርትና የስልክ አገልግሎት ያሟለ፣
  • ከተመሳሳይ ደረጃ ት/ቤቶች ተገቢ ርቀት ያለው፡፡

የምድረ ግቢው ገጽታና አደረጃጀት

  • ዙሪያው ግንብ አጥር የተከለለ፣
  • ብሎኮችና ክፍሎች ለትምህርት ሥራ አመቺ ሆነው የተሠሩ፣
  • ለመኪና ማቆሚያ፣ ለመዝናኛ ሜዳ ያለውና ለክፍል ውጪ ትምህርት ተስማሚ ቦታ ያለው

የምድረ ግቢው ስፋት

  • ከ3000 ካሬ ሜትር በላይ ስፋት ያለው ግቢ ላይ የሰፈረ

የሕንፃው አሠራርና አደረጃጀት

  • ሕንፃዎቹና ክፍሎቹ ከብሎኬት፣ የተሠሩና ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው፣
  • እያንዳንዱ ክፍል 7.75 x 6.75 የሆነ የመማሪያ ክፍል ያለው፣
  • ልዩ ልዩ የአስተዳደር ክፍሎች ያሉት፣
  • የቤተመጻሕፍት፣ የትምህርት ማበልፀጊያ ማዕከል፣ የቤተሙከራ ክፍል፣ የቴክኒካል ድሮዊንግ ክፍልና የካምፒውተር ክፍሎች ያሉት፣
  • የሠራተኞችና የተማሪዎች መፀዳጃ በየጾታው ያለው፣
  • የመሰብሰቢያ አዳራሽና የሻይ ክበብ ያሟላ ነው፡፡

የቤተመጻሕፍት ውስጥ አደረጃጀት

  • በየትምህርት ዓይነት ለየክፍል ደረጃው የሚመጥኑ በቂ ቁጥር ያላቸው የማጣቀሻና የተማሪው መጻሕፍት፣
  • በቂ ቁጥር ያላቸው የመጻሕፍት መደርደሪያዎች፣
  • ኮምፒውተሮች፣ ካርታዎች፣ የአማርኛና የእንግሊዝኛ ቋንቋ መዝገበ ቃላት፣ ኢንሳይክሎፒዲያዎችና ልዩ ልዩ ቻርቶች፣
  • ለክፍሉ ሠራተኞች አገልግሎት የሚውል ጠረጴዛና ወንበር፣
  • በሙያው የሰለጠነ ሠራተኛ ያለው፡፡

የትምህርት ማበልፀጊያ ማዕከል አደረጃጀት

  • ለወርክሾኘና ለዕቃ ማስቀመጫ የሚያገለግል ክፍል፣
  • ለወርክሾኘ አገልግሎት የሚውሉ ልዩ ልዩ መሣሪያዎች፣
  • በቂ የሆኑ ወንበሮችና ጠረጴዛዎች፣
  • በሙያው ችሎታ ያለው መምህር ያሟላ ነው፡፡

የቴክኒካል ድሮዊንግ ክፍል አደረጃጀት

  • ለሥራው የሚያገለግል በቂ ክፍል ያለው፣
  • ለሥራው የሚያገለግሉ ወንበሮችና ጠረጴዛዎች ያሉት፣
  • ለሥራው የሚያገለግሉ ልዩ ልዩ መሣሪያዎች ያሉት፡፡

የኮምፒውተር ክፍል አደረጃጀት

  • ለኮምፒውተር አገልግሎት የሚውል ክፍል፣
  • በቂ ኮምፒውተሮች ከነሙሉ አክሰሰሪአቸው፣
  • በቂ ወንበሮችና የኮምፒውተሮች ማስቀመጫ ጠረጴዛዎች፣
  • የማስታወቂያ ሰሌዳ፣
  • በሙያው የሠለጠነ መምህር ያለው፣
  • ሙሉ ኢኒተርኔት አገልግሎት /ብሮድ ባንድ/ ለተማሪዎች ለአስተማሪዎችና ከቢሮዎች ጋር የተያያዘ የ24 ሰዓት አገልግሎት

የቤተሙከራ ክፍል አደረጃጀት

  • ለ3ቱም ሣይንስ ዘርፎች የሚያገለግሉ ደረጃቸውን የጠበቁ የቤተሙከራ ክፍሎች፣
  • ለቤተሙከራው አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች፣ መሣሪያዎችና ኬሚካሎች፣
  • የውሃና የኤሌክትሪክ አገልግሎት፣
  • የመምህሩና በቂ የተማሪዎች ዲሞኒስትሬሽን ቴክሎች ስቱሎች፣
  • ለቁሳቁሶች፣ ለመሣሪያዎችና ለኬሚካሎች ማስቀመጫ የሚያገለግሉ በቂ ካፖርዶች፣
  • የሰለጠኑ የላቦራቶሪ ቴክኒሽያኖችን የሟላ መሆኑ፡፡

የመምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ሁኔታ

  • ለሁሉም ትምህርት ዘርፎች በሙያው የሰለጠኑ የመጀመሪያ ዲግሪና በላይ ያላቸው 34 ቋሚ ቅጥር መምህራን፣
  • የ2ኛ ዲግሪና ሥልጠና ያለው ቋሚ ር/መምህር ዋና እና ም/ር/መምህር፣
  • ከር/መምህራን ጀምሮ በልዩ ልዩ ክፍሎች የማያገለግሉ የሰለጠኑ ቋሚ ሠራተኞች ተመድበው የሚሠሩ፡፡

በብሔራዊ ፈተናዎች ያለው ውጤታማነት

  • ለተከታታይ 6 ዓመታት 1ዐኛ ክፍል ሲያስፈትን የዘንድሮን ሳይጨምር ለፈተና ከቀረቡት ጠቅላላ ተማሪዎች በአማካይ 98.8% ለመሰናዶ ትምህርት የማብቃት ሪከርድ ያለው፣
  • ለ4 ዓመታት የመሰናዶ ተማሪዎችን ያስፈተነ ሲሆን የዘንድሮን ሳይጨምር ጠቅላላ ከተፈተኑት ተማሪዎች 100% ለከፍተኛ ትምህርት እንዲበቁ አድርጓል፡

የስፖርት ሜዳዎች

  • ደረጃውን የጠበቀ የእጅ ኳስ ሜዳን፣ የመረብ ኳስ ሜዳን የያዘ
  • ሙሉ መሣሪያዎች ኳሶች፣ ለዚሁ አገልግሎት የሚውል መሳሪያ የተሟላለት

የተለያዩ ክበባት

  • የቤተክርስቲያንህን እወቅ
  • የስርዓተ ፆታ ክበብ
  • የተለያዩ ዲፓርትመንቶች ክበብ
  • የፀረ ኤድስ ክበብ
  • ስነ-ዜጋና ስነምግባር ክበብ
  • የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ
  • የሚኒ ሚዲያ ክበብ ከነ ቢሮውና ከነመሳሪያዎቹ

እነዚህ ክበባት የቢሮ በአባላት የተደራጀና ሙሉ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ተግባራዊ ለውጥ እየመጡ ያሉ ናቸው

የትምህርት አሰጣጥና የክፍል ክፍል ዝውውር ሁኔታ

  • በሁሉም ክፍል ደረጃና የትምህርት ዓይነት ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የትምህርት ፖሊሲ መሠረት በሙሉ ቀን ኘሮግራም በቀን 7 x 45 ክፍለ ጊዜ የሚስተምርና ሴኩላር የሆነ ትምህርት ቢሮ በሚወስነው የክፍል ክፍል ዝውውር ፖሊሲ መሠረት የሚሠራ፣
  • በየትምህርት ዘመኑ በትምህርት ቢሮ በሚወስነው የክፍል ክፍል ዝውውር ፖሊሲ መሠረት የሚሠራ፣
  • ለየክፍል ደረጃው የሚሰጡ ቴስቶችና ዋና ፈተናዎች በትምህርት ቢሮ ዓመታዊ የትምህርት ካሌንደር መሠረት እየሰጠ የሚገኝ መሆኑ፡፡
  • የመንግስትን ሥርዓተ ትምህርት ጠብቆ ሳያጓድል የሚሠራ፣
  • የተማሪ ክፍል ጥምርታ የትምህርት ጥራትን አስቦ የተደራጀ፣