በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን 6ኛውን የፓትሪያርክ ምርጫ የካቲት 21/2005 ዓ.ም እንደምታካሂድ አስታወቀች፡፡

February 8, 2013

                                በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ

7

ድስተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ለማስመረጥ የተቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ ከምርጫው ሂደት ጋርና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ በተመለከተ ዛሬ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም ለጋዜጠኞች ወቅታዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

በዚሁም መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን 6ኛ የፓትሪያሪክ ምርጫ ለማካሄድ ቅዱስ ሲኖዶስ በወሰነው መሠረት ከሊቃነ ዻዻሳት ፣ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰራተኞች ከአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ከሰንበት ትምህርት ቤቶች እና ከማህበረ ቅዱሳን የተውጣጣ 13 አባላት ያለው አሰመራጭ ኮሚቴ አቋቋማ ዝግጅት ሰታደረግ መቆየቷ ይታወቃል፡፡

በዚሁም መሠረት ኮሚቴው ምርጫው የሚካሄድበት ቀንና የምርጫውን ፕሮገራም በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል ፡፡ የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢና የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ ብፁዕ አቡነ እሰጢፋኖስ በመግለጫው እንዳሉት የመጨረሻውን ምርጫ የሚያከናውኑት ከሊቃነዻዻሳት፣ ከገዳማትና አድባራት፣ ከካህናት፣ ከምዕመናን፣ ከሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና ከማሀበረ ቅዱሳን የተውጣጡ በአጠቃላይ 800 ሰዎቸ ናቸው ብለዋል፡፡

የምርጫውን ሂደት ለማስፈጸም የወጣው መግለጫ ምእመናን ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከአጥቢያ ቤተ ክርስቲያናቸው ማንነታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ በመያዝ ለእጩነት የሚያስቡትን አባት አስመራጭ ኮሚቴው ጽ/ቤት ድረስ በአካል በመቅረብ እንዲሁም ከሀገር ውጪ የሚገኙ በፋክስ ቁጥር 0111567711 እና 0111580540 ከየካቲት 1 እስከ 8 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲጠቁሙ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

አስመራጭ ኮሚቴው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባዔ የካቲት18/2005 ዓ.ም አምስት እጩዎችን ይፋ ያደርጋል ፡፡ ምርጫውን ለማካሄድ ከ53 አህጉር ስብከት፣ ከካህናት፣ ከምዕመናን፣ ከሰንበት ተማሪዎች የተውጣጡ 13 አባላት ተመርጠው የካቲት 19 አዲስ አበባ እንደሚገቡም አስታውቀዋል፡፡

ምርጫው የሚካሄድበት ቀንም የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ምርጫው ተከናውኖ፣ በዚሁ ዕለት ምሽት 12 ሰዓት ላይ ውጤቱ ለሕዝቡ ይፋ እንደሚደረግ አስታውቋል፡፡ ምርጫው የዓለም አብያተክርስቲያናት ማህበር፣ የአፍሪካ አብያተክርስቲያናት ምክር ቤት ተወካዮች እና ምዕመናን እንደሚታዘቡትም ገልፀዋል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ የወደደውንና የፈቀደውን ቤተ ክርስቲያንን የሚመራ አባት በመንበሩ ያስቀምጥ ዘንድ ካህናትና ምእመናን ከየካቲት 1 እስከ 8 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ አምላካቸውን በጸሎት እንዲጠይቁ ለአንድ ሱባኤ የሚቆይ የጸሎት ጊዜ መታወጁን አስታውቋል፡ የፓትርያርኩ በዐለ ሲመቱም እሁድ የካቲት 24/2005 ዓ.ም በመንበረ ጸበዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚካሄድም አስታውቀዋል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/7.jpg 389 519 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2013-02-08 18:07:122013-02-08 18:07:12የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን 6ኛውን የፓትሪያርክ ምርጫ የካቲት 21/2005 ዓ.ም እንደምታካሂድ አስታወቀች፡፡

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን ለ4ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን ለ4ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ... Link to: ሰበር ዜና Link to: ሰበር ዜና ሰበር ዜና
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top