በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መሠረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም ሥልጠና ተጀመረ

April 3, 2013

0020
የካቴድራሉ ሠራተኞች ሥልጠናውን ሲከታተሉ

በሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በካቴድራሉ አስተዳደር አማካኝነት መሠረታዊ የኮምፒውተር ትምህርት /ሥልጠና በካቴድራሉ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለካቴድራሉ ጽ/ቤት ሠራተኞች እና ለተወሰኑ ማህበረ ካህናት ከመጋቢት 20/07/2005 ዓ.ም ጀምሮ ሥልጠናው በመካሄድ ላይ ነው፡፡

የሥልጠናው ዋና አስተባባሪ መ/ር ዘሩ ብርሃኔ እንደተናገሩት፤ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ትምህርት ማስተማር ዘመኑን የዋጀ መንፈሳዊና መኅበራዊ አገልግሎት መስጠት ያስችላል በመሆኑም ትምህርቱን እየተከታተሉ ያሉ የከቴድራሉ ሠራተኞች በኮምፒውተር ትምህርት መሠልጠናቸው የመረጃ ሥርዓትና ተዛማጅ ሥራዎች በዘመናዊ መልክ ለማከናወን እንደሚያግዛቸውም ተናግረዋል፡፡ የካቴድራሉ ጽ/ቤት ሥልጠናውን አዘጋጅቶ የካቴድራሉ አባቶች ካህናትና የጽ/ቤት ሠራተኞች በአንድነት እንዲሠለጥኑ ማድረጉ ቤተ ክርስቲያንን በልማት ለማሳደግ ያለውን ርእይ እንደሚያሳይ ጠቁመው፤ ወደፊትም የተለያዩ ሲስተሞችን ለምሳሌ

  • የሰበካ ጉባኤ አባላት መመዝገቢያ ሶፍት ዌር፣
  • የመዝገብ ቤት ፋይል መያዣ ዳታ ቤዝ ሶፍት ዌር፣
  • ኤች አር ሲስተም/HRS/፣
  • እስታስቲካዊ የሆኑ የጋብቻ፣
  • የልደት እና የመሳሰሉ ሲስተሞችን አዘጋጅቶ ሠራተኞች በቀላሉ መደበኛ ሥራቸውን በፍጥነትና በጥራት ማከናወን እንዲቺሉ በባለሞያዎች ሥልጠና ሊሰጥ እንደሚቺል ተናግረዋል ፡፡

የመጀመሪያውን ዙር መሠረታዊ የኮምፒዩተር ሥልጠና እየተከታተሉት ያለው ሥልጠና/ የትምህርት ዓይነት

  • አጠቃላይ ስለ ኮምፒዩተር መግቢያ /Introduction to computer/IT
  • ኤም ኤስ ዊንዶውስ (Ms-wodows /Window XP /7)
  • ማክሮሶፍት ወርድ 2007/10/ Micro soft office word 2007/10
  • ማይክሮሶፍት ኤክሲኤል 2007/10/ Micro soft office excel 2007/10
  • ማይክሮሶፍት አክሰስ 2007/10/ Micro soft office access 2007/10
  • ማይክሮሶፍት ፓወር ፖይንት 2007/10/ Micro soft office PowerPoint 2007/10
  • ማይክሮሶፍት ፐብሊሸር 2007/10/ Micro soft office publisher 2007/10
  • የኢንተርኔት አጠቃቀምና
  • አጠቃላይ ቴክኖሎጀው ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና መኅበራዊ አገልግሎት ያለው ጠቀሜታ የተመለከተ መሆኑን አስተባባሪ ጠቁሞው፣ ሥልጠናው ሠራተኞች አገልግሎታቸውን በተቀላጠፈ ሁኔታ ለመሥራት እንደሚረዳ እና በአጣቃላይ ዘመኑ/ትክኖሎጂው የደረሰበትን ደረጃ እና የአሰራር ሄደት ለሠራተኞች በወቅቱና በሰዓቱ ማስተዋወቁ ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ሥልጠናውን ለ2 ወራት ያህል እየሰጡ ያሉት አሠልጣኞች በአሁኑ ጊዜ በኮምፒዩተር ሳይንስ/በአይቲ ሙያ በተለያዩ ተቋማት የሚያስተምሩ/የሚሠሩ አባላት እንደሆኑ አስተባባሪው አስረድቷል፡፡ ለወደፊትም ሥልጠናውን ከካቴድራሉ በተጨማሪ ወደ ሌሎች መሰል አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት እና መሥራቤቶች በመሔድ ለሚመለከታቸው ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሠረተኞች ይህን የመሰል ሥልጠና መስጠቱ ተገቢ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የኮምፒዩተር ሥልጠናው ካለቀ በኋላም በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ሲፈቀድ ሌሎች ሥልጠናዎች ማለትም የአስተዳደር እና የሒሳብ አያያዝ ሥልጠናዎች በካቴድራሉ ሊሰጡ እንደሚቺሉ ጠቁመዋል፡፡

የካቴድራሉ አስተዳደር ቀደም ሲል ከ2 ዓመት በፊት ዘመናዊ ድረ ገጽ/ዌብ ሳይት ያሰራ ሲሆን ከ3 ዓመት በፊት በ2ኛ ደረጃ ት/ቤት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያለው የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት ከካቴድራሉ ጋር ከ500 ሜትር በላይ የሆነውን ርቀት በኔትዎረክ በማገኛት በአሁኑ ሰዓት የካቴድራሉ ጽ/ቤት ሙሉ በሙሉ የብሮድ ብንድ ኢንተርኔት አገልግሎት ለሠራተኞች መስጠት መጀመሩ አስተዳደሩን እጅግ የሚያስመሰገን የሥራ ውጤት ነው፡፡

ይህም ካቴድራሉን ጨምሮ የካቴድራሉን ሙዝዬም፤የካቴድራሉ ዘመናዊ ት/ቤት በማስተዋወቅ እና ካቴድራሉ በልማቱ በኩል ለሚያደርው እንቀስቃሴ በመላው ዓለም ላይ ከሚገኙ የዕምነቱ ተከታዮች ምዕመናን ጋር እንደ አንድ ሚዲያ ሆኖ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ቴክኖሎጂ የካቴድራሉ አስተዳደር በቀላሉ ት/ቤቱን ለመቆጣጠር፤መረጃን በቀላሉ ለመለዋጥ እና ፕሪንተርና የመሳሰሉትን ሼር ለመድረግ እንዲሁም የሠረተኛውን አቅም በመገንበታ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው፡፡

በሌላ ዜና የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መጋቢት 18 እና 19 ቀን 2005 ዓ.ም በጊዮን ሆቴል ለ318 በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሥር ለሚሠሩ ሰባኪያነ ወንግል በሙስና ዙሪያ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ሰባኪያነ ወንጌሉ ሙስናን በመከላከል ረገድ በሕብረተ ሰቡ ውስጥ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ የ2 ቀን ሙሉ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/0020.jpg 480 640 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2013-04-03 07:13:022013-04-03 07:13:02በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መሠረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም ሥልጠና ተጀመረ

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከወላጆች ጋር በመማር መስተማር ሄደት ላይ ውይይት ተካሄደ Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከወላጆች ጋር በመማር መስተማር ሄደት ላይ ውይይት ተካሄደ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል መሰናዶ... Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ሁለተኛና መሰናዶ ት/ቤት ዓመታዊ የእግር ኳስ ስፖርት ውድድር ተካሄደ Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ሁለተኛና መሰናዶ ት/ቤት ዓመታዊ የእግር ኳስ ስፖርት ውድድር ተካሄደ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ሁለተኛና...
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top