በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት ኃላፊዎች ከብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአ/አ/ሀ/ስ/የቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀጳጳስና ከአ/አ/ሀ/ስ/ዋና ስራ አስከያጅ ጋራ የትውውቅ መርሃ ግብር ተካሄደ

June 23, 2013

                    በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ

md1

ሰኔ 14/2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 2.30 ጀምሮ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ የትውውቅ መርሃ ግብሩ የተካሄደ ሲሆን በዚሁ ዕለት አዲሱ አስከያጅ መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአ/አ/ሀ/ስ/የቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀጳጳስ አማካኝነት /ጋባዥነት ራሳቸውን እንዲያስተዋውቁ በተፈቀደላቸው መሠረት በአጭሩ ከጀመሪያ ጀምሮ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አሰከያጅነት እሰከ ተሶሙበት የነበረውን ሁኔታ ለተሰብሳቢዎች ገልፀዋል፡፡አያይዘውም ዕለቱን የገልፅልያል ብለው ያሰቡትን ከመጽሐፍ ቅዱስ 2 ጥቅሶችን አንብበዋል፡፡

ክቡር ዋና ስራ አስከያጁ መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት እንደተናገሩት ለዚሁ ትልቅ ሐዋሪያዊ አገልገሎት በተሻለ መልኩ እንዳገለግል ለመረጡኝ መንፈሳዊያን አበቶቼ በተለይም ታላቁ የልማትና የሰላም አባት የሆኑትን ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን እንዳላሳፍር ድንግል ማርያም በሽልም ታውጣህ ብላችሁ ፀልዩልኝ ብለዋል፡፡

አቅማቸው በፈቀደው መልኩ /መጠን የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ለማስፈፀም ሌት ተቀን ሊሠሩ እንደሚችሉ ገልፀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ኃላፊዎችና ሠራተኞችም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስረሰ አሰከያጅ ሆነው በመሾማቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀውላቸዋል ፡፡

በአጠቃላይ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና የገዳማትና አድባራት ሠራተኞች በሊቀ ጳጳሱ በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ እና በዋና ስራ አስከያጁ በመጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መመደብ እጅግ በጣም ከመደሰታቸውም በላይ ሙስና እና ብልሹ አሠራርን በማስወገድና በማጥፋት ከፍተኛ የሆነ ሥራ ሊሠሩ ሁሉም ሠራተኞች ከፍተኛ የሆነ ተስፋ እንደጣሉባቸው ገልፀውላቸዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአ/አ/ሀ/ስ/የቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀጳጳስ በበኩላቸው እንደተናገሩት ወደ ባህሩ ገብተን እ በንዋኛልን ወይም ደግሞ እንሰጥማለን ምክያቱም ከኋላ ሆነው የሚታዘቡን ብዙ ናቸው ብለዋል፡፡በመሆኑም የተጣለብንን ከፍተኛ ኃላፊነት ለመወጣት በባለሞያዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አወቃቀርና አደረጃጀት፡-

1ኛው ከሐምሌ 1/2005 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ወራት ያህል የሚገለግል ጊዚያዊ የሥራ አደረጃት እስከ መስከረም 30/2006 ዓ.ምሥራ ላይ የሚውል ሲሆን

2ኛው ሙሉ መዋቅርና አደረጃጀት ደግሞ ሥራውን ሙሉ ቡሙሉ ተጠናቅቆ ከጥቅምት 1/2006 ዓ.ም ጀምሮ በባለሞያዎች ተጠንቶና ተሠርቶ የቀረበውን በሚመለከታቸው አካላት ተገምግሞና ተስተካክሎ ሥራ ላይ እንደሚውል ጠቁመዋል፡፡

md2

በመሆኑም ሥልጠኑን ወደ ታች በማውረድና የተሻለ አቅም ያላቸው ሰዎችን በቦታው ላይ በመስቀመጥ ሥራው ሊሰራ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ በዚሁም መሠረት አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በ7 ክፍለ ከተሞች ተደራጅተው ከሐምሌ 1/2005ዓ.ም መደበኛ ሥራቸውን መሥራት እንደሚጀምሩ ገልፀው ገዳማቱና አድባራቱ ራሳቸው የሚገለገሉባቸው በመሆኑ አቅማቸው በፈቀደው መልኩ በፍላጎትና በውዴታ የተለያዩ ቁሳቁሶችን መርዳት ብትችሉ መልካም ነው ባሉት አባታዊ ማሳሰቢያ መሠረት ፡-

1. 113 የሚሆኑ ገዳማትና አድባራት 1,158,900.00

2. 9 የሚሆኑ ገዳማትና አድባራት ሙሉ የሥራ አስኪያጆች (የሥራ ኃላፊዎች) ወምበርና ጠረጴዛ

3. 11 ገዳማትና አድባራት ዘመናዊ ኮምፒውተር ከነ ፕሪንተሩ

4. 11 ገዳማትና አድባራት ለክፍል ሠራተኞች ወምበርና ጠረጴዛ

5. 2 ገዳማትና አድባራት 2 ትላልቅ የአበባ ምንጣፎች

6. 1 ደብር 10 ወምበሮች እስከ ሰኔ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ሁሉም ነገር አጠቃልለው ለሀገረ ስብከቱ ገቢ እንደሚያደርጉ ቃል የገቡ ሲሆን አሠራሩን ግልጽ ለማድረግ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ተወካዮች ቁሳቁሶቹን ለመግዛት በጉባዔው ተመርጠዋል፡፡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአዲስ መልክ የሚደራጁ የክፍለ ከተሞቹ ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ይሆናል፡፡

1. አራዳ ክፍለ ከተማ 2. አቃቂ ክፍለ ከተማ 3. ቦሌ ክፍለ ከተማ 4. ጉለሌ ክፍለ ከተማ 5. ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ 6. ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ እና 7. የካ ክፍለ ከተማ ናቸው፡፡

{flike}{plusone}

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/md1.jpg 480 640 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2013-06-23 17:25:072013-06-23 17:25:07የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት ኃላፊዎች ከብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአ/አ/ሀ/ስ/የቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀጳጳስና ከአ/አ/ሀ/ስ/ዋና ስራ አስከያጅ ጋራ የትውውቅ መርሃ ግብር ተካሄደ

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ አረጋወያን ለ9ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ Link to: በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ አረጋወያን ለ9ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ... Link to: ዓመታዊው የዓጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በዓል በድምቀት ተከበረ Link to: ዓመታዊው የዓጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በዓል በድምቀት ተከበረ ዓመታዊው የዓጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በዓል በድምቀት...
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top