በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2006 ዓ.ም.የ2006 ዓ.ም. ዐብይ ጾምን አስመልክቶ ቃለ ምዕዳን አስተላለፉ

February 24, 2014

0908

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2006 ዓ.ም. ዐቢይ ጾም አስመልክቶ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ ባሉበት ወቅት “ጾም ለመንፈሳዊ ሕይወት መጎልበት፣ ራስን ለመግዛት፣ ከእግዚአብሔር ጋር ልዩ ግንኙነትና አንድነት ለመፍጠር እጅግ አስፈላጊ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ዐብይ ጾሙን አስመልክቶ ያስተላለፉትን ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይመልከቱ፡፡
መልእክት ዘእም ኀበ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በእንተ በዓለ ጾም ዓቢይ ዘእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት፡፡
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

በሀገር ውስጥም ኾነ በውጭ የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ፡-
እግዚአብሔር አምላክ እንኳን ለ፳፻፮ ዓ.ም. የጌታችን የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችኁ፡፡
‹‹ወእመሰ በምግባረ መንፈስ ቀተልክምዎ ለምግባረ ነፍስትክሙ ተሐይዉ ለዓለም፤ በመንፈሳዊ ሥራ ሥጋዊ ሥራችኹን ብትገድሉ ለዘላለሙ ትድናላችኹ፡፡›› /ሮሜ ፰÷፲፫/
ጾም ከጥንት ጀምሮ በዘመነ ብሉይም በዘመነ ሐዲስ የተወደደ፣ የፈቃደ ሥጋ መቆጣጠሪያ፣ የፈቃደ ነፍስ ማበልጸጊያ መሣርያ ነው፤ እነሙሴ፣ እነኤልያስ እና እነዳንኤል ከእግዚአብሔር ጋራ በቀጥታ ይገናኙ የነበረው ራሳቸውን በጾም ለእግዚአብሔር በማስገዛት ነው፡፡

ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዓርባ መዓልትና ዓርባ ሌሊት ጾሞ፣ በሰይጣን የቀረበለትን ፈተና አሸንፎ፣ የጾምን ድል አድራጊነት በተግባርና በትምህርት አሳይቶናል፤ (ማቴ. ፬÷፩ -፲፩)
ቅዱሳን ሐዋርያትም እግዚአብሔር ሥራቸውን እንዲያቃናላቸው፣ ኃይለ መዊዕ (የአሸናፊነት ኃይል) እንዲሰጣቸው በየጊዜው ይጸልዩ ነበር፤ (ግብ. ሐዋ. ፲÷፳፫)
ሐዋርያዊት፣ ጥንታዊትና ህልውት በኵሉ የኾነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም ከነቢያት፣ ከጌታችንና ከሐዋርያት በተማረችው ትምህርትና በተቀበለችው ትውፊት መሠረት ከእግዚአብሔር ጋራ ለመገናኘት፣ ኃይለ አጋንንትን ድል ለማድረግ፣ ከእግዚአብሔር በረከትንና ረድኤትን ለማግኘት ጾምን ትጾማለች፡፡
ሰው በተፈጥሮው እርስ በርስ የሚጋጩ ኹለት ፍላጎቶች በውስጡ እንዳሉ ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል፤ እነዚኽ ፍላጎቶች ሥጋዊና መንፈሳዊ ተብለው የሚታወቁ ሲኾን፣ የሥጋ ፍላጎት ለነፍስ ፍላጎት፣ የነፍስ ፍላጎትም ለሥጋ ፍላጎት ተቃራኒ እንደኾነ በቅዱሳት መጻሕፍት ተብራርቶና ተገልጾ ተቀምጦአል፡፡ (ገላ. ፭÷፲፮-፲፰)
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን በተመለከተ ሲያስተምር ‹‹የሥጋ ፍላጎት ሞትን ያመጣል፤ የነፍስ ፍላጎት ግን ሰላምንና ሕይወትን ይሰጠናል፤›› ብሏል፤ (ሮሜ ፮÷፮-፰)
የጾም አስፈላጊነት የሚመነጨውም ከዚኽ መሠረታዊ ትምህርት ነው፡፡ ሥጋ ኃይልና ሙቀት ሰጪ ምግቦችን አብዝቶ በተመገበ ቁጥር ኃይል ይሰማዋል፤ በዚኽ ጊዜ ለእግዚአብሔር መታዘዝን ይዘነጋል፤ ወንድሙን ለመበደል ይፈጥናል፤ ማመዛዘን አይችልም፤ ብዙ ስሕተትንም ይፈጽማል፤ በመጨረሻም ይሞታል ማለትም ከእግዚአብሔር ጋራ አንድነትን ያጣል፤ በመንፈሳዊ እይታ ከእግዚአብሔር አንድነት መለየት እጅግ በጣም የከፋ ሞት ነው፡፡
በአንጻሩ ደግሞ ሰው ከምግብ በታቀበ ጊዜ ረጋ ብሎ ማሰብን፣ ማስተዋልን፣ ማመዛዘንን፣ ለእግዚአብሔር መታዘዝን፣ ራስን መግዛትን፣ ርኅራኄንና ቸርነትን፣ ለወንድም አዛኝነትን ገንዘብ ያደርጋል፤ በመጨረሻም ከእግዚአብሔር ጋራ አንድነቱን ያጠነክራል፤ በዚኽም የሞት አሸናፊ ኾኖ በእግዚአብሔር መንግሥት በዘላለማዊ ሕይወትና ክብር ተደስቶ ይኖራል፤
ከዚኽ አኳያ ጾም ለመንፈሳዊ ሕይወት መጎልበት፣ ራስን በመግዛት ከእግዚአብሔር ጋራ ልዩ ግንኙነትና አንድነት ለመፍጠር እጅግ አስፈላጊ ኾኖ ይገኛል፡፡
ጾማችን በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት አግኝቶ ሙሉ ዋጋ ሊያሰጠን የሚችለው ከፍቅር፣ ከምጽዋት፣ ከሰላም፣ ከጸሎትና ራስን ለእግዚአብሔር ከማስገዛት ጋራ ሲኾን ነው፡፡

የተወደዳችኹ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቼ ምእመናንና ምእመናት!

በፍጹም ሓሳባችን፣ በሙሉ ኃይላችንና በፍጹም ልቡናችን ለእግዚአብሔር በምንገዛበት በዚኽ ወቅት ካለን ሀብት ከፍለን፣ በየሰፈሩ የሚገኙ ጧሪ የሌላቸው አረጋውያንን፣ አሳዳጊ የሌላቸው ሕፃናትን፣ ሠርተው ራሳቸውን መርዳት ያልቻሉ አካል ጉዳተኞችን በመርዳት ጾሙን ልንጾም ይገባል፡፡
ወርኃ ጾም በመንፈሳዊ ሕይወታችንም በሥጋዊ ኑሯችን ከምንም ጊዜ በበለጠ ግዙፍና ታላላቅ ሥራዎችን ሠርተን የምናጠናቅቅበት ጊዜ ሊኾን ይገባል፡፡
በተለይም በመንፈሳዊ ሕይወታችን ለእግዚአብሔር ያለንን ተገዥነት ለማረጋገጥ፣ በመንፈስና በጽድቅ ኾነን በየቀኑ አብዝተን የምንጾምበትና የምንሰግድበት ሊኾን ይገባል፡፡
በሥጋዊ ኑሯችንም ሥራ ከሚያስፈቱን ነገሮች ኹሉ ርቀን ቀኑን በሙሉ በሥራ ላይ የምናውልበት ሊኾን ይገባል፡፡ በመኾኑም ሕዝበ ክርስቲያኑ በአገራችን የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ለማሳካት አፈርን የመገደብና መስኖን የማስፋፋት ሥራ አጠናክሮ እንዲሠራና ወርኃ ጾሙን በላቀ የሥራ ርብርብ እንዲያሳልፍ መልእክታችንን ከአደራ ጭምር እናስተላልፋለን፡፡

በመጨረሻም፡-

እግዚአብሔር አምላክ ወርኃ ጾሙን መልካም የንስሐ፣ የሰላም፣ የፍቅርና የሥራ ጊዜ አድርጎ በማስፈጸም ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላምና በጤና እንዲያደርሰን በጾምና በጸሎት እንትጋ በማለት መልእክታችንን በድጋሚ እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝባችንን ይባርክ ይቀድስ አሜን!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.

{flike}{plusone}

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/0908.jpg 425 640 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2014-02-24 05:11:262014-02-24 05:11:26ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2006 ዓ.ም.የ2006 ዓ.ም. ዐብይ ጾምን አስመልክቶ ቃለ ምዕዳን አስተላለፉ

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: የ2006ዓ.ም የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከበረ Link to: የ2006ዓ.ም የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከበረ የ2006ዓ.ም የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከበረ Link to: ዕለታተ ሰሙነ ሕማማት Link to: ዕለታተ ሰሙነ ሕማማት ዕለታተ ሰሙነ ሕማማት
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top