በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

የብፁዕ አቡነ አረጋዊ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ

January 9, 2015

d4250

የብፁዕ አቡነ አረጋዊ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ሓላፊ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ሲያገለግሉበት በነበረው በዚሁ ታላቅ ካቴድራል ቅዱስ ፓትርያርኩ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመምሪያ ሓላፊዎች፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን በተገኙበት ተፈጸሟል፡፡
ከጸሎተ ፍትሐቱ በኋላ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በሰጡት ቃለ ምእዳን “ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ሕይወታቸውን ሁሉ ለእግዚአብሔር የሰጡ፤ እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ፤ ሲያከብሩ የኖሩ፤ ሃይማኖትን ጠብቀው ያስጠበቁ አባት ነበሩ” ብለዋል፡፡

በሥርዓተ ቀብራቸው የተነበበው የብፁዕነታቸው የሕይወት ታሪክ እንደሚከተለው እናቀርባለን፡-
ዜና ሕይወቱ ወሞቱ ለብፁዕ  አቡነ አረጋዊ ሊቀ ጳጳስ
1. ብፁዕ አቡነ አረጋዊ በ1901 ዓ.ም ተወልደው እድሜአቸው ለትምህርት ሲደርስ ትምህርት ቤት ገብተው ንባብና ዳዊት ተምረው እንዲሁም እስከ ፀዋትወ ዜማ ያለውን የቤተ ክርስቲያናችንን ትምህርት አጠናቅቀው ከብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ግብጻዊ ዲቁና እና መዓረገ ክህነት ተቀብለዋል፡፡ ወደ ዋልድባ አብረንታት ገዳም ሔደው ከ1933 እስከ 1942 ዓ.ም ድረስ ለዘጠኝ ዓመታት ያህል ሥርዓተ ገዳሙን ከአጠኑ በኋላ በዚሁ ታላቅ ገዳም መዓረገ ምንኩስናን ተቀብለው በደብረ ዓባይ ገዳም የደብረ ዓባይ መዝገበ ቅዳሴ ዜማን ተምረው ለመምህርነት በቅተዋል፡፡
2. በ1943 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ትእዛዝ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማትን እንዲያገለግሉ ወደ ኢየሩሳሌም ተልከው ለ4 ዓመታት ያህል ካገለገሉ በኋላ በቅዱስ ፓትርያርኩ ፈቃድ ወደ ግብፅ ሔደው ለ16 ዓመታት ያህል የዓረብኛ ቋንቋና ነገረ መለኮትን ተምረዋል፡፡
3. ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በሱዳን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን በኃላፊነት ለማገልገል ተልከው ለ6 ዓመታት ያህል አስተዳዳሪ ሁነው ሠርተዋል፡፡ በዚሁም ኃላፊነት ሳሉ በ1968 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ሁነው በተሾሙ ጊዜ በሱዳን የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያንን ወክለው በመምጣት ለበዓሉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
4. በ1972 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ወደ ሀገራቸው ተመልሰው በቅዱስ ፓትርያርኩ ፈቃድ የመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊቀ ሥልጣናት ተብለው በማስተዳደር ላይ እያሉ በ1983 ዓ.ም በሱዳን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሾመዋል፡፡
5. ከመጋቢት 1985 ዓ.ም ጀምሮ የኢሉባቦርና ጋምቤላ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ለአንድ ዓመት ያህል ሠርተዋል፡፡
6. ከየካቲት 1986 ዓ.ም ጀምሮ የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳምና ት/ቤት የበላይ ኃላፊ ሆነው ሲሠሩ ቆይተዋል፡፡
7. ከሐምሌ 1986 ዓ.ም ጀምሮ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ሠርተዋል፡፡
8. ከግንቦት 1992 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ ተዛውረው የመንበረ ጸበዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ኃላፊ ሆነው እንዲሠሩ ተደርጓል፡፡
በመጨረሻም በዚሁ ሥራ ላይ ሳሉ ባደረባቸው ድንገተኛ ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም በተወለዱ በ106 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል፡፡ በቀብራቸውም ሥነ ሥርዓት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ባሉበት፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ካህናት ተገኝተው በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት ጸሎተ ፍትሐቱ ከተፈጸመ በኋላ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የብፁዕነታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጽሟል፡፡

{flike}{plusone}

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/d4250.jpg 346 461 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2015-01-09 16:18:582015-01-09 16:18:58የብፁዕ አቡነ አረጋዊ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የ2007 ዓ.ም.የልደት በዓልን አስመልከቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የ2007 ዓ.ም.የልደት በዓልን አስመልከቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ... Link to: እንኳን ለአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ አመታዊ ክብረ በአል በሰላም አደረሳችሁ Link to: እንኳን ለአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ አመታዊ ክብረ በአል በሰላም አደረሳችሁ እንኳን ለአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ አመታዊ...
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top