የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የ2011 ዓ.ም የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ300 ችግረኞች እርዳታ ሰጠ!!

 “እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ” 2ኛ ቆሮ.9÷7

በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምግባረ ሠናይ ክፍል መሪነት እና አስተባባሪነት ለ300 አረጋወያን ዘላቂና ለተወሱኑ ወራት ሊያቆይ የሚችል ለእያንዳንዳቸው በአይነት15 ኪሎ ፍርኖ ዱቄት፣3 ሌትር ዘይት እና 3 ኪሎ ስኳር ተሰቷል፡፡

ካቴድራሉ 15 አረጋወያን በመደበኛነት የሚጦራቸው ያሉት ሲሆን ከዚሁ በተጨማሪ ምእመናንን በማስተባበር ሁልጊዜ በየዓመቱ የትንሣኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ከአራዳ ክፍል ከተማ ወረዳ 9 ችግረኛ መሆናቸውን ተገልፆ ዝርዝራቸው በደብዳቤ የተላኩና እንደዚሁም ችግረኛ መሆናቸውን በአጥቢው በተዋቀረው ኮሚቴ ተጠንቶ ዝርዝራቸው ለቀረቡ ችግረኞች እርዳታው ይሰጣል፡፡

ዝርዝር መረጃውን በሚቀጥሉት ሳምንታት እናቀርባለን፡፡

ማሳሰቢያ

 የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምግባረ ሠናይ አረጋውያን መርጃ መዕከል ይምጡና ይጎብኙ!!
አድራሻ፡-4 ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ገቢ ውስጥ ከሙዝዬሙ ጀርባ
ስ.ቁ. :-0912 66 26 88/011-1-23-35-18
ኢ-ሜል ፡- eotcht@gmail.com
ድረ-ገጽ፡- www.trinity.eotc.org.et
ዘወትር ከሰኞ- እሁድ በካቴድራሉ የእለት ገንዘብ መቀብያ እየመጡ ለካቴድራሉ አረጋውያን ብለው መክፈል ይችላሉ ወይም በኢትያጵያ ንግድ ባንክ የቁጠባ ሒሳብ ቁጥር ፡- 1000010560318 ይክፈሉ፡፡