በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለአስተዳደር ሠራተኞች የአስተዳደር ሥልጠና ተሰጠ

ኅዳር 16/03/2012 ዓ.ም በካቴድራሉ አስተዳደር ጽ/ቤት ለውጥ /Change management በሚል ርዕስ የአንድ ቀን ሥልጠና ተሰቷል፡፡
ሥልናውን የሰጡት በዚሁ ሙያ ላይ የረጅም ጊዜ አገልግሎት ያላቸው የሰበካ ጉባኤ አባል የሆኑት አቶ ደረጃ ተክሌ ናቸው፡፡

አስተዳደራዊ ለውጥ ቤተ ክርስቴያን ያስፈልጋል፤ ቀደም ሲል የነበሩ የቤተ ክርስቲያን አባቶችና መሪዎች ለሀገሪቱ እና ለቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን በስፋት ያብራሩት አቶ ደረጃ እንደ አባቶቻችን ለሀገራችንና ለቤተ ክርስቲያናችን ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ እና ለሰው ልጅ ሁሉ ስለአንድነት ዘወትር ማስተማር እንደሚገባ፤ አንድነቱም ከራሳችን ነው መጀመር ያለበት እኛ አንድ ሳንሆን ሌላውን አንድ ማድረግ አንችልም፤ የትኛውንም ችግር ያለ አንድነት ሊፈታ አይችልም ብለዋል፡፡

በዘርና በፖለቲክ መለያት አግባብ አይደልም፤ በተለይም በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ሁሉም ሰው የእግዚአብሔር ፍጡር ሆኖ ሳለ በዘርና በፖለቲካ ተለያይቶ ማየት እጅግ ያሳፍራል ብለዋል፡፡
ከቴድራሉ ዓለም አቀፍ እንደመሆኑ መጠን በእስትራቴጂክ ፕላን እና በእቅድ መመራት ይኖርበታል ፤አሰራራችን በሻሻልን እና በለወጥን ቁጥር ካቴድራሉንና የካቴድራሉ ማኅበረ ሰብ እንዲሁም ተገልጋዩን ማኅበረ ላይ ጥሩ ተነሳሽነትን ይፈጥራል ብለዋል፡፡
ካቴድራሉ የቱሪስት መስህብ ቢሆንም ለቱሪስት የተመቻቸ ሁኔታ ባለመኖሩ የሚጠበቅበትን ያህል አይደልም፤ ደረጃውን የጠበቀ ቤተ መጻህፍትም የለውም፤በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶበት ሊሠራ ይገባል ብለዋል፡፡
የካቴድራሉ አስተዳደር ሠራተኞችም በበኩላቸው ሥልጠና አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ይህን መሰል ሥልጠና በየሥራ ዘርፉ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ሃሳባቸውን ገልፀዋል፡፡

የዚህ ዓይነት ሥልጠና ቀደም ሲል በካቴድራሉ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመምህንና ለልዩ ልዩ ሠረተኞች እንደተሰጠ ይታወሳል፡፡