በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

ታሪክ

August 27, 2011

የስብከተወንጌል አጀማመር

  • ወንጌልን (የምስራቹን ቃል) መስበክ የጀመረው ራሱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ማቴ. 4፣17

በደዌ ሥጋ የታሠሩትን በመፈወስ በደዌ ኃጢአት የተያዙትን ከኃጢአት በማንፃት የመንግሥቱን ወንጌል ሰበከ፡፡ ሐዋርያትን ሰብስቦ ካስተማራቸው በኋላ ወደ ዓለም ሁሉ እንዲሄዱና ወንጌልን እንዲሰብኩ ያዘዛቸው እሱ ነው፡፡ ማቴ. 28፣19 ማር. 16፣15

ስብከተወንጌል በሐዋርያት ዘመን

ቅዱሳን ሐዋርያት የተሰጣቸውን አምላካዊ ትዕዛዝ በደስታ ተቀብለው የሰው ዘር ባለበት ሁሉ እየሄዱ ቃለ ወንጌልን ሰበኩ፣ በስሙ አጋንንትን አወጡ፣ ድውያንን ፈወሱ፣ ሙታንን አስነሡ፣ የወንጌል ብርሃን በዓለም ሁሉ እንዲበራ አደረጉ፡፡

ስብከተወንጌል በሐዋርያውያን አበው ዘመን

በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተው በሐዋርያት የተስፋፋው ስብከተ ወንጌል ከሐዋርያት ቀጥለው በተነሡ አበውም በነአግናጥዮስ፣ በነአትናቴዎስ፣ በነዮሐንስ አፈወርቅ፣ በነቅዱስ ቄርሎስ፣ ወ ዘ ተ  በሕይወት መስዋዕትነት ጭምር ተሰብኳል፡፡ ይህን ለወደፊቱ በቤተክርስቲያን ታሪክ የትምህርት ዓምድ ይጠብቁን፡፡

ስብከተወንጌል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

  • ይህን የምሥራች ቃለ ወንጌል ኢትዮጵያ አምና የተቀበለችው ገና በዚየው በኢየሩሳሌም አከባቢ እየተሰበከ በነበረበት ዘመን በ34ኛው ዓመተ ምሕረት መሆኑ በቅዱስ መጽሐፍ ላይ ስለተጻፈ  ሁሉም የተረዳው ጉዳይ ነው (ግ/ሐ/8፣26-4ዐ)

በዚህ መሠረት የኢ/አ/ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዛሬም እንደትናንቱ ወንጌለ መንግሥተ ወልደ እግዚአብሔርን በሐዋርያዊ ትጋት እየሰበከች ትገኛለች

ስብከተወንጌል አሁን ባለንበት ዘመን

አሁን እየኖርንበት ባለው በሀያ አንደኛው ምዕት ዓመት የስብከተወንጌል አገልግሎት በዓለም ዙሪያ ለመቃኘት (ለጠቅላላ ግንዛቤ) በቀጣዩ እንሄድበታለን፡፡ በኛ በኢትዮጵያችን ግን ምን ጊዜም ለኢትዮጵያውያን የዕውቀት መሠረት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕንፃ ቤተክርስቲያኑ ባለበት ቦታ ሁሉ (ከሰውና ከፋይናንስ ዕጥረት የተነሣ ከተወሰኑ አካባቢዎች በስተቀር) የስብከተወንጌል አገልግሎት ይካሄዳል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png 0 0 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2011-08-27 09:37:312011-08-27 09:37:31ታሪክ

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: አውደ ወራዙት (ወጣትነት በቤተክርስቲያን) Link to: አውደ ወራዙት (ወጣትነት በቤተክርስቲያን) አውደ ወራዙት (ወጣትነት በቤተክርስቲያን) Link to: ዝቋላ ገዳም Link to: ዝቋላ ገዳም ዝቋላ ገዳም
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top