የ2006 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በድምቀት ተከበረ

2006

የመስቀል ደመራ በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘ ኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘ አክሱም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤የአዲስ አበባ መስተዳድር ከንቲባ ተወካይ፤ የተለያዩ ሀገራት ከፍተኛ ዲፕሎማቶችና አንባሳደሮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጥንግ ድርብ የለበሱ ሊቃውንት፣ ካህናትና ምእመናን በተገኙበት በደማቅ ስነ-ስርአት ተከብርዋል፡፡

በዓሉ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትሪያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፀሎተ ቡራኬ የተጀመረው የተጀመረ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ተቀብሮ የነበረውን እና በንግስት እሌኒ የተገኘውን መስቀል ለማሰብ በዓሉን እንደሚያከብሩት ፤ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተናግረዋል።

ቅዱስነታቸው ኢትዮጵያውያን የተገኘውን መስቀል በማሰብ የመስቀሉን በረከት ለማግኘት እንደሚያከብሩትም ነው የተናገሩት። የመስቀል በዓል ለዘመናት ኢትዮጵያውያን በጋራ ሲያከብሩት የቆዩት በዓል መሆኑን ያወሱት ቅዱስነታቸው ፤ ህዝቦች ተከባብረውና ተቻችለው ለመኖራቸው ተምሳሌት መሆኑንም አስረድተዋል። በመሆኑም የመስቀል በዓል በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ የሚደረገው ጥረትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የአዲስ አበባ ከንቲባ የአቶ ድሪባ ኩማ ተወካይ በመክፈቻ ንግግራቸው የመስቀል ደመራ በአል የሀገራችን ብሄር ብሀሄረሰቦችና ህዝቦች ለዘመናት በድምቀት ሲያከብሩት የኖሩት ሃይማኖታዊ በአል ብቻ ሳይሆን ታሪካችንን፣ የቱሪዝም ሀብቶችንና ሌሎች እሴቶቻችን ለሌላው ዓለም የምናስተዋውቅበት የማንነታችን መገለጫ ጭምር ነው ብለዋል፡፡

በበአሉ ጥንግ ድርብ የለበሱ ካህናቶችና የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተለያዩ ዝማሬዎችን አቅርበዋል። የደመራ መለኮስ ስነ ስርአቱ ተካሂዶ የደመራው በአል ፍጻሜ ሆኗል ፡፡

ለተጨማሪ ንባብ እዚህ ላይ ይጫኑ (‹‹የብፁዕ ወቅደስ አቡነ ማትያስ ቀዲማዊ ፓትርያርክ መልእክት››)

{flike}{plusone}