በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን ለ3ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ

02

ከአሁን በፊት በዌብሳይታችን አማካኝነት ወጣት ብሩክ አስራት ከዛሬ 3 ወር በፊት ጀምሮ ለካቴድራሉ አረጋውያን የሚሆን በየወሩ ለአረጋውያኑ የሚያስፈልጋቸውን የምግብ እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ስንዘግብ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን አሁንም እንደተለመደው ለ3ኛ ጊዜ ለገና በዓል መዋያ የሚሆን፡-

   25 ሌትር ጋዝ፤

    15 ሌትር ዘይት

   15 ኪሎ ስኳር፤

   15 ኪሎ በርበሬ፤

    15 ኪሎ ሽሮ፤5 ፓኬት ሻይ ቅጠል

    5 ኪሎ ጨው፤3 ኪሎ ቅቤ እና 20 ሰሙና

 

በእነ ወ/ሮ ማርታ ወርቄ፤በወንድሙ፤በወጣት ዳዊት መስፍን እና በጓደኞቹ አማካኝነት እርዳታውን የላከ ሲሆን ከ2 ሳምንት በፊት በወ/ሮ ማርታ ወረቄ፤በወ/ሮ ሮማን እሸቴ፤በወ/ሮ የምስራች አበበና በወጣት ዳግማዊ መስፍን አማካኝነት የአረጋውያኑ መኖሪያ ቤት የሆነውን የንግስት ዘውዲቱ መታሰቢያ ቤት አንድ ቀን ማጽዳታቸው ይታወቀል፡፡ በመሆኑም ወጣት ብሩክ አስራት ላደረገው ነገር ሁሉ ምስጋናችን እጅግ የላቀ መሆኑን እየገለፅን ሌሎችም የዚሁ የተቀደሰ ዓላማ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያቸን እናስተላልፋለን መልካም የገና እና የጥምቀት በዓል እንዲሆንላችሁም ከልብ እንመኛለን፡፡