በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ አረጋወያን ለ7ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ

“ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው እግዚአብሔር ከክፉ ያድነዋል፡፡” መዝ. 40÷1

“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ”2ኛ ቆሮ. 9÷7

0002

ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ በድህረ ገፃችን አማካኝነት ወጣት ብሩክ አስራት የክርስትና ስሙ ግርማ ጽዮን ከዛሬ 7 ወር በፊት ጀምሮ ለካቴድራሉ አረጋውያን የሚሆን በየወሩ ለአረጋውያኑ የሚያስፈልጋቸውን የምግብ እርዳታ እያደረገላቸው መሆኑን ስንዘግብ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን አሁንም እንደተለመደው ለ7ኛ ጊዜ ለ1 ወር የሚሆን በእነ ወ/ሮ ማርታ ወርቄ፤በወንድሙ እና በጓደኞቹ አማካኝነት እርዳታውን ልኳል፡፡

በዚሁ ዕለት ቄሰ ገበዝ አባ ገ/ዮሐንስ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቄሰ ገበዝ አማካኝነት ለወጣት ብሩክ አስራት፤ለቤተሰዎቹና ለጓደኞቹ ጸሎትና ምስጋና እንዲሁም ቃለ ምእዳን ተሰጥተዋል ፡፡ በወጣት ብሩክ አስራት እየተደረገ ላለው ነገር ሁሉ ምስጋናቸው እጅግ የላቀ መሆኑን ገልፀው ሌሎችም የዚሁ የተቀደሰ ዓላማ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በመጨረሻም ቄሰ ገበዝ አባ ገ/ዮሐንስ ለወጣት ብሩክ አስራትና ለቤተ ሰዎቹ እያደረገው ላለው ነገር ሁሉ በዓጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ስም ካቴድራሉን በመወከል ምስጋናቸውን አቅርበዋል ፡፡

እነዚህ አረጋውያን ከዛሬ 45 ዓመታት በፊት ከዐፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት ጀምሮ በንጉሱ አማካኝነት በካቴድራሉ በጎ አድራጎት /ምግባረ ሠናይ ክፍል ሥር በቃለ ዓዋዲ መሠረት የተቋቋመ ሲሆን ቀደም ሲል በብዙ መልኩ የተደራጀ እንደነበር የሚነገር ሲሆን አሁንም በካቴድራሉ አስተዳደር አማካኝነት እንደቀድሞ ለማጠናከር ከፍተኛ የሆነ ጥረት እየተደረገ ነው በመሆኑም በዘላቂነተ የአረጋውያኑ ችግር በመጠኑ ለመቅረፍ እንደ ወጣት ብሩክ አስራት የክርስትና ስሙ ግርማ ጽዮን አቅማችሁ የፈቀደውን/የቻላችሁትን ያህል እርዳታ እንድታድርጉ እናሳስባለን፡፡ አረጋውያኑ ከሚያስፈልጓቸው መሠረታዊ ነገሮች መካከል፡-

  1. ምግብ፣
  2. መጠለያ፣
  3. ንጽህና፣
  4. ልብስና
  5. ሞግዚት ሲሆኑ የቦታው ጉዳይ በተመለከተ አሁን አረጋውያኑ ያሉበት ቤትና አጠገቡ ያለውን ቦታ ከካቴድራሉ ጽ/ቤት ጋር በመነጋገርና በማስፈቀድ በዘመናዊ መልኩ ቤቱ መሥራት ከመቻሉም በላይ አቅም በፈቀደ መጠን ተጨማሪ ረዳት አልባ አረጋውያንና ሕፃናት መርዳት ይቻላል፡፡

{flike}{plusone}