በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቅጽረ ግቢ ጸረ ተዋህስያን ኬሚካል ተረጨ

በነገው ዕለት ለሚከበረው ወርሃዊው የአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ በካቴድራሉ
አስተዳደር አማካኝነት የተለያዩ የኮረና በሽታ ቅድመ መከላከያ የሚያገለግሉ 3 የሙቀት መለኪያ፣ 54 ሌትር
ሳኒታይዘር፣ 30 የአካባቢው ወጣቶች የሚያስተናግዱበት መለያ ልብስ ተገዝቶ ለአገልግሎት የተዘጋጀ ሴሆን
የጸረ ተዋህስያን ኬሚካል መርጨት መርሐ ግብሩም በሃሌሉያ ከፍተኛ ክሊኒክ የጤና ባለሙያዎች አማካኝነት እንዲከናወን ተደርጓል።

መልካም በዓል ያድርግልን።

አስከፊ በሽታውም አብርሃሙ ሥላሴ ከኢትዮጵያ ሀገራችንንና ከዓለማችን ያርቁልን።