በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሠራተኞች የአስተዳደርና የቅርስ አያያዝ ስልጠና ተሰጠ

                          በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ

መስከረም 18/01/05

  ይህ ስልጠና የተዘጋጀው በካቴድራሉ አስተዳደር ጽ/ቤት አማካኝነት ሲሆን ለዚሁ ስልጠና እንዲሰጡ የተጋበዙ ምሁራን አሰልጣኞች፡-

1ኛ. ዶ/ር አባ ኃለማርያም መለሰ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዲን

2ኛ. መ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ የቅርሳቅርስና ቤተመዘክር ኃላፊ ሲሆኑ በተቀመጠላቸው መርሃ ግብር መሠረት በተሠጣቸው ርዕስ ስልጠናውን/ትምህርቱን በሚገባ ሰጥተዋል/አስተምረዋል

የአስተዳደርና የቤተ ክርስቲያን አገልገሎት በተመለከተ ስልጠናውን የሰጡት ዶ/ር አባ ኃለማርያም መለሰ ሲሆኑ ለ3 ሰዓታት ያህል ሰፋ ያለ ስልጠና ለካቴድራሉ ካህናትና ልዩ ልዩ ሠራተኞች ሰጥተዋል የካቴድራሉ ሠራተኞችም የተሰጣቸውን ስልጠና አስመልክተው በሰጡት አስተያየት ካቴድራሉ ዘመኑ የሚፈቅደውን የአስተዳደር ስልጠና መስጠቱ ወቅታዊና ተገቢ መሆኑን ጠቁመው ለተደረገላቸው ነገር ሁሉ የካቴድራሉ አስተዳደርና አሠልጣኙ ዶ/ር አባ ኃለማርያምን ከልብ አመስግነዋል በቀጣይም ስልጠናው በየደረጃው መቀጠልና መጠናከር እንዳለበት አስተያየተቸውን ሠጥተዋል ከዶ/ር አባ ኃለማርያም ቀጥሎ ስለ ቅርስ ምንነትና አያያዝ በተመለከተ ስልጠናውን የሰጡት መ/ር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ሲሆኑ ስለ ቅርስ ምንነትና አያያዝ በተመለከተ ሰፋያለ ጊዜ ወስደው ስልጠናውን ሠጥተዋል በተለይም ለኢትዮጵያ መኩሪያ የሆነው ይህ ካቴድራል በኢትዮጵያ ደረጃ በቅርስና በታሪክ ባለቤትነቱ ደረጃውን እንደጠበቀ ሲሆን አሁንም እነደቀድሞው ሁሉ ታሪክ በማስመዝገብ ላይ መሆኑን ገልፀዋል በመጨረሻም ይህ የኢትዮጵያ መኩሪያ የሆነውን ካቴድራል ሁላችንም በሚገባ መያዝና ምከባከብ ይኖርብናል በማለት ስልጠናውን አጠናቀዋል በቀጣይም ካቴድራሉ በሚጠይቀው /በሚፈልገው መልኩ ስለ ቅርስ አያያዝ በተመለከተ ስልጠና ለመስጠት ዝግጁ እንደሆኑም ለካቴድራሉ ሠራተኞች ገልፀዋል፡፡

 

የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሠራተኞች ስልጠናውን ሲካፈሉ በከፊል የሚያሳይ ፎቶ ግራፍ