የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ልዩ እድሳት እንደሚያስፈልገው ተገለፀ፡፡

                   በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ

የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሰበካ ጉባኤ አስተዳደር /ቤት እንደገለፀው የካቴድራሉ ህንፃ ወስጣዊም ሆነ ውጫዊው ክፍሉ ከጊዜ ብዛት የተነሳ የመሰነጣጠቅ ሁኔታ እየታየበት በመምጣቱ አስቸኳ የሆነ ሙሉ እድሳት እንደሚያስፈልገውና ጥናቱ በጥንቃቄ እንዲጠና ከበላይ አካልም ጭምር ስለታነበት በባለሞያዎች በምን ዓይነት ሁኔታ መታደስ እንዳለበት ከመጋቢት 2ዐዐ4 ዓ.ም ጀምሮ ጥንቃቄ በተሞላበት ሙሉ ጥናት ሲደረግበት ቆይቶ ሕዳር 15/03/2005 ዓ.ም ዶ/ር ብፁእ አቡነ ገሪማና ብፁእ አቡነ አረጋዊ በተገኙበት ለካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ አስተዳደር፤ለካቴድራሉ ልማት ኮሚቴና ለተለያዩ ምሁራን በነኢንጂነር ቀሲስ ደመቀ አማካኝነት ሙሉ ጥናቱ ቀርቧል፡፡ካቴድራሉ ለማደስ የባለሙያዎች አስተዋጽኦ ወሳኝ በመሆኑ በአስተዳደሩ አማካይነት የተለየዩ አዳዲስ ባለሙያዎች በልማት ኮማቴው እንዲሳተፉ ተደርጎ ካቴድራሉ በምን መልኩ መታደስ እንዳለበት ሰፊ ጥናት ሲያደርጉ ቆይቷል በማድረግ ላይም ናቸው፡፡ ውጤቱ ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ለካቴድራሉ ሰበካ ጉባዔና ልማት ኮሚቴ እንዲሁም ለተለያዩ ምሁራን የቀረበ ሲሆን ቀደም ሲል ጥናቱ ለቅዱስ አባታችን በሕይወት እያሉ ቀርቦ ጥሩ አድናቆት ተችሮት እንደነበር ከአንዳንድ የካቴድራሉ ሠራተኞች ለማወቅ ተችሏል፡፡ በገቢ ማሰባሰቢያ ረገድም በካቴድራሉ አውደ ምህረት ሲነገረ የቆየ ሲሆን በተለይም መጋቢት 1 ቀን 2ዐዐ4 . እና ሰኔ 24 ቀን 2ዐዐ4 . በካቴድራሉ ሁለገብ አዳራሽ የስብከተ ወንጌልና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር ተካሂዶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ከዚህም በተጨማሪ በካቴድራሉ ዌብ ሳይትና በካቴድራሉ ዐውደ ምህረት ላይ በሰፊው ሲገለጽ መቆየቱም አይዘነጋም፡፡

   

ልማትን በተመለከተ

 

በአሁኑ ወቀት የካቴድራሉን ሁለንተናዊ ችግር ሙሉ በሙሉ ይፈታል ተብሎ የተገመተው በ22 ማዞሪያ አካባቢ በ47,ዐዐዐ,ዐዐዐ.ዐዐ (አርባ ሰባት ሚሊዮን ብር) አዲስ ባለ አራት ፎቅ ዘመናዊ ሁለገብ ሕንፃ እያስገነባ ሲሆን ነገር ግን ሥራው ቀደም ሲል ከ3 ዓመታት በፊት መሬቱ እንዳይወሰድ ሲባል ብቻ የተጀመረ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ግን ያን ያህል ገንዘብ አግኝቶ ሥራውን ለመሥራት ካቴድራሉ እጅግ በመቸገሩና ከአቅሙ በላይ በመሆኑ ከባለቤቶቹ ምእመናን ጋር በመወየየትና የተለያዩ አማራጮችን በማመቻቸት ላይ ይገኛል፡፡በመሆኑም ጉዳዩ የሁሉም ምእመን ጉዳይ በመሆኑ ምእመንበገንዘባቸውና በእውቀታቸው የቻሉትን የህል የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ቤተክርስቲያኒቱ ጥሪዋን በማስተላለፍ ላይ ትገኛለች፡፡

           

 

የካቴድራሉ መቃብር ሥፍራ ከዓመታት በፊት በማለቁ ምክንያት ምእመናን በመቸገር ላይ መሆናቸው ለሁላችን ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም ጊዜያዊ መፍትሔ ይሰጥ ይሆናል ተብሎ በካቴድራሉ ቅፅረ ግቢ በብር 7ዐዐ,ዐዐዐ.ዐዐ (ሰባት መቶ ሺህ ብር) ወጭ ዘመናዊ የቀብር ፉካ እያሰራ እያሠራ ቢሆንም ዘላቂ መፍትሔ ለማግኘት ግን በመቃብር ዙሪያ የሚያጠና ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራውን በመሥራት ላይ ሲሆን ከአርበኞች ጋርም የቤተ ክርስቲያኒቱና የህዝበ ክርስቲያኑ ችግር ሊፈታ በሚችል መልኩ በሰፈው እየተመካከሩበት ይገኛል ፡፡በመሆኑም ምእመናን ሐሳባቸውና አስተያየታቸው እንዲሁም ምን መሠት እንዳለበት በአካልና በካቴድራሉ ዌብ ሳይት ባለው አድራሻ መጠቀም የበኩላቸውአስተዋፅኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

 

  በአጠቃላይ ካቴድራሉን በየትኛውም ዘርፍ መርዳት ለሚፈልጉ ምእመናን በአካልና በካቴድራሉ ውብሳይት ባለው    አድራሻና የባንክ አካውንት መጠቀም ካቴድራሉን ለማደስ መርዳት የምችሉ መሆኑንና እንዲሁም በካቴድራሉ ጽ/ቤት በአካል እየመጡ ችግሩን እያዩ የሚስፈልገውን ማቴሪያልም ይሁን ገንዘብ የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል፡፡