በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ አረጋወያን ለ6ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ

                          በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ

“ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፡፡” መዝ. 40÷1

“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ”2ኛ ቆሮ. 9÷7

0014

ከዚህ በፊት በዌብሳይታችን አማካኝነት ወጣት ብሩክ አስራት የክርስትና ስሙ ግርማ ጽዮን ከዛሬ 6 ወር በፊት ጀምሮ ለካቴድራሉ አረጋውያን የሚሆን በየወሩ ለአረጋውያኑ የሚያስፈልጋቸውን የምግብ እርዳታ እያደረገላቸው መሆኑን ስንዘግብ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን አሁንም እንደተለመደው ለ6ኛ ጊዜ ለ1 ወር የሚሆን በእነ ወ/ሮ ማርታ ወርቄ፤በወንድሙ እና በጓደኞቹ አማካኝነት እርዳታውን የላከ ሲሆን ከ4 ወር በፊት በወ/ሮ ማርታ ወረቄ፤በወ/ሮ ሮማን እሸቴ፤በወ/ሮ የምስራች አበበና በወጣት ዳግማዊ መስፍን አማካኝነት የአረጋውያኑ መኖሪያ ቤት የሆነውን የንግስት ዘውዲቱ መታሰቢያ ቤት አንድ ቀን ሙሉ ማጽዳታቸው ይታወቀል፡፡

አሁንም ከአገር ቤት ተመልሶ ወደ አሜሪካ ከሄደ በኋላ ቀደም ሲል ቃል በገባው መሰረት ለ6ኛ ጊዜ ለአንድ ወር የሚሆን የወር አስቤዛ በወንደሙና በጓደኞቹ አማካኝነት እርዳታውን ልኳል፡፡ በዚሁ ዕለት ሊቀ ጠበብት ዘለዓለም መንግስቱ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ም/ስብከተ ወንጌል እና የትምህርት ክፍል ኃላፈ አማካኝነት ለወጣት ብሩክ አስራት፤ለቤተሰዎቹና ለጓደኞቹ ጸሎትና ምስጋና እንዲሁም ቃለ ምእዳን ተሰጥተዋል ፡፡

ሊቀ ጠበብት ዘለዓለም መንግስቱ እንደገለፁት እንደ እነዚህ የመሰለ አቅመ ደካማ የሆኑ አረጋውያን መርዳትበእግዚአብሔር ዘንድ ወጋው እጅግ በጣም ትልቅ መሆኑን ገልፀው በተለይም በካቴድራሉ ቅፅረ ግቢ በንግስት ዘውዲቱ መታሰቢያ ቤት ተጠልለው የሚኖሩ አረጋውያን ለ24 ሰዓታት እግዚአብሔር ሲለምኑ የመኖሩና እግዚአብሔር በሰዎች ላይ አድሮ የዕለት ጉርስ ከሚሰጥዋቸው ምዕመናን ውጭ ምንም ዓይነት ረዳት እንደሌላቸውና በአንዲት ጠባብ ቤት እስከ 8 የሚሆኑ አረጋውያን እናቶች ተጨናንቀው እንደሚኖሩና የምግብ ችግር ብቻ ሳይሆን የመፀዳጃ፤የማዕድ ቤት፤ የውሀና የንጽህና ችግርም እንዳለባቸው ገልፀዋል ፡፡

0018

በወጣት ብሩክ አስራት እየተደረገ ላለው ነገር ሁሉ ምስጋናቸው እጅግ የላቀ መሆኑን ገልፀው ሌሎችም የዚሁ የተቀደሰ ዓላማ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በመጨረሻም በሊቀ ጠበብት ዘለዓለም መንግስቱ አማካኝነት ለወጣት ብሩክ አስራትና ለቤተ ሰዎቹ እያደረገው ላለው ነገር ሁሉ በዓጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ስም ካቴድራሉን በመወከል ምስጋናቸውን አቅርበዋል ፡፡

እነዚህ አረጋውያን ከዛሬ 45 ዓመታት በፊት ከዐፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት ጀምሮ በንጉሱ አማካኝነት በካቴድራሉ በጎ አድራጎት /ምግባረ ሠናይ ክፍል ሥር በቃለ ዓዋዲ መሠረት የተቋቋመ ሲሆን ቀደም ሲል በብዙ መልኩ የተደራጀ እንደነበር የሚነገር ሲሆን አሁንም በካቴድራሉ አስተዳደር አማካኝነት እንደቀድሞ ለማጠናከር ከፍተኛ የሆነ ጥረት እየተደረገ ነው በመሆኑም በዘላቂነተ የአረጋውያኑ ችግር በመጠኑ ለመቅረፍ እንደ ወጣት ብሩክ አስራት የክርስትና ስሙ ግርማ ጽዮን አቅማችሁ የፈቀደውን/የቻላችሁትን ያህል እርዳታ እንድታድርጉ እናሳስባለን፡፡

The Holy Trinity Cathedral charity was established during the time of Emperor Haileselassie. It is still in existence helping the needy. During the time of the former king, he was providing Fund worth enough to feed and cloth the poor. But after the dethronment of the Emperor, things have become different and the charity run out of funds as a result of which the needy are in dire shortage to provide the necessary provisions. It would be worthwhile to make clear that those of you who have the interest of extending help for the subsistence of the service of the charity. The church we in advance express our indebtedness of any contribution. At present the charity assistances 15 aged and helpless women.