በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ሁለተኛና መሰናዶ ት/ቤት ዓመታዊ የእግር ኳስ ስፖርት ውድድር ተካሄደ

ጨዋታው በሁለት ምድብ ተከፍሎ በሁለተኛና መሰናዶ ተማሪዎች መካከል በወንዶችና በሴቶች በ21 ሴክሽን መካከል የተካሄደ ሲሆን ይኸውም ዘጠኝ ሴክሽን የሁተለኛ መሰናዶ ተማሪዎች ሲሆኑ 12 ሴክሸን ደግሞ የመሰናዶ ተማሪዎች ናቸው፡፡

በዚሁም መሠረት የሁለተኛ ደረጃ የዘጠኝ ሴክሸን አሸናፊ የ1ዐA ክፍሎች ተማሪዎች ሲሆኑ የ12 ሴክሽን አሸናፊ 12B ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ በዚህ ውጤት መሠረት የ1ዐA አንድ ዋንጫና የ3ዐዐዐ ብር ተሸላሚ ሲሆኑ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል አሸነፊዋች የ12B ክፍል የ12ዐዐ.ዐዐ ብር እና በመሰናዶ ት/ቤቱ ስም የአንድ ዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

በዚህ ውጤት መሠረት የሁለተኛ ደረጃ ተመሪዎችን ወክለው የተጫወቱት የ1ዐA ክፍል ተማሪዎች የ12B ክፍልን 5 ለ 1 በሆነ ውጤት የአሻናፊዎች አሸናፊ በመሆን የ2ዐዐ5 ዓ/ም የሁለት ዋንጫ ተሸላሚ በመሆን በት/ቤቱ ውስጥ መምህራንና ተማሪዎች በአንድ ላይ በመሆን ደስታቸውን ኬክ በመቁርስ ለትምህርት ቤቱ ማኅበረ ሰብና ለተማሪዎች ደስታቸውን ገልጸዋል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የወንዶች ኮካብ ተሸላሚ የሚካኤል አረጋይ 12c ክፍል የ100 ብር ተሸላሚ ሲሆን ኮከብ ተጨዋች ቢኒያም ኑር የ100 ብር ሲሆን ኮካብ ተጨዋች ሴቶች ከ12B ክፍል ኪብሩን ተሻገር የ100 ብር ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

የፀባይ ዋንጫ ተጨዋች የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ በሴቶች በሁለኛና በመሰናዶ ተማሪዎች የእግር ኳስ ጨዋታ የመሰናዶ ተማሪዎች ሁለት ለባዶ በሆነ ውጤት ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን አሸንፈዋል፡፡ በዚሁ ውጤት የመሰናዶ ሴት ተማሪዎች አንድ ዋንጫ አንስተዋል እንዲሁም የቅርጫት ኳስ ውድድር በ12D ክፍል የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ተማሪዎች በመሸነፍ የዓመቱ የአሸናፊ አሸናፊ አንድ ዋንጫ አግኝተዋል፡፡

በዚሁ ዕለቱ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳደር፤ የክፍለ ከተማ የስፖርት ክፍል ኃላፊ ፤የተለያዩ የካቴድራሉ ሠራተኞች፤ የት/ቤቱ የአስተዳደር ሠራተኞችና መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች በተገኙበት የአምስት ዋንጫና የ8ዐዐ.ዐዐ ብር የገንዘብ መበረታቻ ሽልማት ለተማሪዎች በክቡር ሊቀ ሥልጣናት አባ ገ/ሥላሴ በላይ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ አማካኝነት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ፡፡

በሌላ ዜና በክፍለ ከተማ ደረጃ በተዘጋጀው የተማሪዎች የፈጠራ ውድድር የካቴድራሉ የ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች በፈጠራ ሥራ 2ኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆኑ እንደዚሁም በክፍለ ከተማ ደረጃ በተዘጋጀው የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በ8ኛ 3ኛ እና በ4ኛ ክፍል 2 ደረጃ ወጥተዋል፡፡ ይህም ት/ቤቱ ምን ያህል ውጤታማ ተማሪዎች እያፈራ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡