በኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
  • ቀዳሚ ገጽ
  • መ/ጸ/ቅ/ሥ/ካቴድራል
    • የአስተዳዳሪው መልእክት
    • ታሪክ
    • አስተዳደራዊ መዋቅር
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • መንፈሳዊ አገልግሎቶች
    • ፎቶዎች
  • ቤተ መዘክር
    • የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ መዘክር
    • ፎቶዎች
  • ት/ ቤት
    • መግቢያ
    • መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ
    • 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • 1ኛ ድረጃ ት/ቤት ወርሐዊ ክፍያ
    • ፎቶዎች
  • ሰንበት ት/ቤት
    • መግቢያ
    • አውደ ወራዙት
    • ፎቶዎች
  • አገልግሎቶች
    • መግቢያ
    • ፎቶዎች
  • ስብከተ ወንጌል
    • መግቢያ
    • ታሪክ
    • ፎቶዎች
  • Menu Menu

የጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር ሥርዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ

April 14, 2017

0296

በኢትዮጵያ አርተዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቀመረ ዲሜጥሮስ አቆጣጠር መሠረት በየዓመቱ ሲከበር የቆየው የጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር በዓል በዘንድሮውም ዓመት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ፓትርያርክ ርዕስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፡፡
ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ልብሰ ተክህኖ በለበሱ ቀሳውስትና ዲያቆናት በየክፍለ ሰዓቱ የተመደበውን ጸሎተ ግብረ ሕማማት በዜማና በንባብ፣ በግእዝና በአማርኛ ቋንቋ አስምተዋል፤ የካቴድራሉ ሊቃውንትም በዓሉን አስመልክቶ በቅዱስ ያሬድ የተደረሰውን ቃል እግዚአብሔር በየክፍለ ጊዜያቱ በዜማ አቅረበዋል ፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ከጧቱ ሦስት ሰዓት ጀምረው በካቴድራሉ በመገኘት አባታዊ ትምህርትና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የደቀመዛሙርቱን እግር እንዳጠበ ቅዱስነታቸውም የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን እግር አጥበዋል፡፡
ቅዱስነታቸው በዚያው በካቴድራሉ ለተሰበሰቡ የተለያዩ ተቋማት የሚድያ ባለሙያዎች በዓሉን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፤ቅድስነታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደጠቆሙት በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ለሚኖሩ የኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት እምነት ተከታዮች   በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆንላቸውና የተቸገሩትን በመርዳት በዓሉን እንዲያከብሩ አሳስበዋል ፡፡
በቅዱስነታቸው መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ እንድርያስ የሊቃውንት ጉባኤ የበላይ ኃላፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል ፤ብፁዕነታቸው ባስተላለፉት ትምህርት በዓሉ የአዲስ ኪዳን ሥርዓት የተጀመረበት ፣ቅዱስ ቁርባን ለሐዋርያት የተሰጠበት፣ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተማሪዎቹን እግር በማጠብ ትህትናን በተግባር ያሳየበት ነው ፤እኛም ከእርሱ ትህትና ልንማር ይገባል ብለዋል ፡፡
በመጨረሻም ቅዱስነታቸው ሥርዓተ ቅዳሴውን በመምራት የበዓሉ ፍጻሜ ሆኖል፡፡

{flike}{plusone}

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/0296.jpg 2136 3216 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2017-04-14 09:46:202017-04-14 09:46:20የጸሎተ ሐሙስ ሕጽበተ እግር ሥርዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ

መፈለጊያ

Search Search

በቅርብ የተለቀቁ

  • የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የንግሥ በዓል በመካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤ/ክ በድምቀት ተከበረ። 
  • ⛪️ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የተቀነጨበ
  • የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
  • ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት የካቴድራሉ እድሳት የሚገኝበት ደረጃ ጉብኝት አድርገዋል። (መስከረም 2017 ዓ.ም)
  • ከእዚህ በላይ ደስታ ምን አለ፤ እንኳን ደስ አላችሁ፤
  • “ቤተ መቅድሳችንን እናድስ ለቀጣዩም ትውልድ እናድርስ ፣ ኃላፊነታችንንም እንወጣ!” መሪ ቃል
  • ሁላችንም የኢትዮዽያ ልጆች ከከተማ እስከ ገጠር ያለን የመ/ጸ/ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጠባቂዎች እና ደጋፊዎች ነን‼️
  • ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመ/ጸ/ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ህንጻ ዕድሳትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ፤
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲፩ኛ ዓመት በዓለ ሢመተ ፕትርክና የካቲት ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይከበራል።
  • የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት

አስተያየቶች

    © Holy Trinity Cathedral | Website by atbiya.com
      Link to: የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ 4ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በድምቀት ተከበረ!! Link to: የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ 4ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በድምቀት ተከበረ!! የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ... Link to: የገብረ ሰላም በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በድምቀት ተከበረ!!! Link to: የገብረ ሰላም በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በድምቀት ተከበረ!!! የገብረ ሰላም በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ...
      Scroll to top Scroll to top Scroll to top