በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን እረዳታ ተሰጠ

          በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ

ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፡፡መዝ. 40¸1

እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ2 ቆሮ. 9¸7

እርዳታውን የሰጠው በአሜሪካን አገር የሚኖረው ኢትዮጵያዊው ወጣት ብሩክ አስራት ነው፡፡ወጣት ብሩክ አስራት አረጋውያኑ የሚኖሩበት የንግስት ዘውዲቱ መታሰቢያ ቤት ተገኝቶ የአረጋውያኑ የአኗኗር ሁኔታ የጎበኘ/የተመለከተ ሲሆን በየሳምነቱ ሰኞ፤ረቡዕና ዓርብ በካቴድራሉ በኩል ለእያንዳንዳቸው 2 እንጀራ እንደሚሰጣቸውና ለዙሁም የተመደበላቸው በጀት 1000 ብር መሆኑን በዲ/ን ዘሩ ብርሃን የካቴድራሉ ም/ሠ/ክ/ኃላፊ አመካኝነት ገለፃ ተደርጓል፡፡

ወጣት ብሩክ አስራት በቀጣይ ቤተሰዎቹና ጓደኞቹን በማስተባበር አቅመ ደካማ የሆኑትን የካቴድራሉ አረጋውያን በተሻለ መልኩ መርዳት እንደሚችል ጠቁሞ ለጊዜው የሚሆን ግን በተሰዎቹ፤ጓደኞቹ፤ዲ/ን ዘሩ ብርሃን የካቴድራሉ ም/ሠ/ክ/ኃላፊ፤ቀሲስ ፀጋዬ ወርቁ የካቴድራሉ ሁለገብ አዳራሽ ክፍል ኃላፊና ቀሲስ መላኩ ጉልላት የካቴድራሉ ሰበካ ጉባዔ አባል በተገኙበት፡-

1. 100 ኪሎ ጤፍ፤

2. 1 ኩንታል ከሰል፤

3. 15 ሌትር ዘይት፤

4. 15 ኪሎ ስኳር፤

5. 15 ኪሎ በርበሬ፤

6. 15 ኪሎ ሽሮ፤

7. 5 ኪሎ ጨው፤

8. 5 ፓኬት ሻይ ቅጠል፤

9. 15 ሰሙና ለአረጋውያኑ እርዳት ሰጥቷል፡፡በመጨረሻም በቀሲስ ፀጋዬ ወርቁ አማካኝነት ለወጣት ብሩክ አስራት ጸሎትና ምስጋና እንዲሁም ቃለ ምእዳን ተሰጥተዋል፡፡

በተያያዘ ዜናም በዲ/ን ይትባረክ ማንያዘዋል አማካኝነት ነዋሪነታቸው በለንደን አገር የሆኑ ወ/ሮ መድኃኒት በለጠ 100 ኪሎ ጤፍ ለካቴድረሉ አረጋወያን አስገዝተው ልከዋል ለወዲፊቱም እንደሚልኩ ቃል ገብተዋል፡፡በስተመጨረሻም የካቴድራሉ አስተዳደር ለተደረገው ነገር ሁሉ ምስጋናው እጅግ የላቀ መሆኑን ገልጾ ሌሎችም የዚሁ የተቀደሰ ዓላማ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡