በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን ለ2ኛ ጊዜ የምግብ እህል እረዳታ ተሰጠ

   

የዛሬ ሁለት ሣምንት አካባቢ ወጣት ብሩክ አስራት ከአሜሪካን አገር መጥቶ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በንግስት ዘውዲቱ መታሰቢያ ቤት ተጠልለው ለሚኖሩ 15 አረጋወያን በአካል ተገኝቶ የአረጋውያኑ የአኗኗር ሁኔታ እንደጎበኘና ለጊዜው የሚስፈልጋቸውን ልዩ ልዩ የአንድ ወር የምግብ አስቤዛ እርዳታ እንዳደረገላቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡

 

 

አሁንም ከአገር ቤት ተመልሶ ወደ አሜሪካ ከሄደ በኋላ ቀደም ሲል ቃል በገባው መሰረት ለሁለተኛ ጊዜ ለአንድ ወር የሚሆን የወር አስቤዛ በወንደሙና በጓደኞቹ አማካኝነት

                   100 ኪሎ ጤፍ፤

                   1 ኩንታል ከሰል፤

                   15 ሌትር ዘይት፤

                   15 ኪሎ ስኳር፤

                   15 ኪሎ በርበሬ፤

                   15 ኪሎ ሽሮ፤

                  5 ኪሎ ጨው፤

                  5 ፓኬት ሻይ ቅጠል፤

                  15 ሰሙና ለአረጋውያኑ እርዳታው እንዲደርሳቸው አድርጓል ፡፡

 

በዚሁ ዕለት በክቡር ሊቀ ሥልጣናት አባ ገ/ሥላሴ በላይ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ አማካኝነት ለወጣት ብሩክ አስራት ቤተሰዎችና ለጓደኞቹ ጸሎትና ምስጋና እንዲሁም ቃለ ምእዳን ተሰጥተዋል ክቡር ሊቀ ሥልጣናት ኣባ ገ/ሥላሴ በላይ እንደገለፁት እንደ እነዚህ የመሰለ አቅመ ደካማ የሆኑ አረጋውያን መርዳትበእግዚአብሔር ዘንድ ወጋው እጅግ በጣም ትልቅ መሆኑን ገልፀው በተለይም በካቴድራሉ ቅፅረ ግቢ በንግስት ዘውዲቱ መታሰቢያ ቤት ተጠልለው የሚኖሩ አረጋውያን 24 ሰዓት እግዚአብሔር ሲለምኑ የመኖሩና እግዚአብሔር በሰዎች ላይ አድሮ የዕለት ጉርስ ከሚሰጥዋቸው ምዕመናን ውጭ ምንም ዓይነት ረዳት እንደሌላቸውና በአንዲት ጠባብ ቤት እስከ 8 የሚሆኑ አረጋውያን እናቶች ተጨናንቀው እንደሚኖሩና የምግብ ችግር ብቻ ሳይሆን የመፀዳጃ፤የማዕድ ቤት፤ የውሀና የንጽህና ችግርም እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡ አያይዘውም እነዚህ አረጋውያን እደሚያቸው ከ75 እስከ 98 ከዚያ በላይ በመሆኑ ራሳቸውን ችለው ምግብ ለማብሰልም ሆነ ለመንቀሳቀስ እንደሚያቅታቸውና ከሚኖሩበት ቤት ለመውጣትም ሆነ ለመግባት እንደሚቸገሩ ገልፀው አረጋውያኑን ልትመግብ፤ ልትንከባከብና ንጽህናቸውን ልትጠብቅ የምትቸል ሰራተኛ እንደሚያሰፈልጋቸው ክቡር ሊቀ ሥልጣናት ገልፀዋል ፡፡በመጨረሻም በወጣት ብሩክ አስራት ለተደረገው ነገር ሁሉ ምስጋናቸው እጅግ የላቀ መሆኑን ገልፀው ሌሎችም የዚሁ የተቀደሰ ዓላማ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡