ዓመታዊው የዓጋዓዝተ ዓለም ሥላሴ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረJanuary 17, 2013 እንኳን ለአብርሃሙ ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና በሕይወት አደረሳችሁ፡፡ በመ/ር ዘሩ እና በመ/ር ዳዊት ‹‹እመ እግዚአብሔር ኢሐነፀ ቤተ ከንቶ ይፃምው እለ የሃንፁ›› ‹‹እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ ግንበኞቹ በከንቱ ይደክማሉ›› መዝ 126፡1 ይህን የታላቁን ነቢይ ቃል ለመነሻነት የተመረጠው ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን የሚከበረው የአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በዓለ ንግሥን ምክንያት ለመግለፅ ነው፡፡ ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ዳዊት ምንም እንኳ ይህን ኃይለ ቃል ከጊዜ በኋላ የፃፈው ቢሆንም የዚህን ጽሑፍ ሐሳብ የሚያንፀባርቀው ቀደም ሲል በዘመነ ህገ ልቡና የተፈፀመ ነበረ በዘፍ1ዐ፡32 ላይ ‹‹የኖኀ የልጆቹ ነገዶች እንደየ ትውልዳቸው በየህዝባቸው እነዚህ ናቸው፤ አህዛብም ከጥፋት ውኃ በኋላ በምድር ላይ ከነዚህ ተከፋፈሉ››፡፡ ይልና በተለይ በዘፍ 11፡1 ጀምሮ ያለውን ስንመለከት ደግሞ ‹‹ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋ ንግግር ነበረች›› ብሎ የሰናኦርን ግንብ መገንባትና መፍረስን ያትታል፡፡ በአጭሩ የዚህ ኃይለ ቃል ጭብጥ ሐሳብ፡- የሰው ልጆች እግዚአብሔርን ለመቃወም ሲሉ ታላቅ ግንብ እንደገነቡና እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ታላቅ ግንብ እንደ አፈራረሰባቸው ነው የሚያብራራው፡፡ ይህን ግንብ ለመገንባት 43 ዓመት ፈጅቶባቸዋል፡፡ ይህ ግንብ በአሁኑ ዘመን በነዱባይ ከተገነቡት ታላላቅ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች እንደሚበልጥ የቤተ ክርስቲያኒቱ መምህራን ይናገራሉ፡፡ ይህንን ህንፃ ሲገነቡ የነበሩ ሰዎች ቀደም ሲል እንደተገለፀው ለትምክህትና እግዚአብሔርን ለመቃወም ስለሆነ እግዚአብሔር ደግሞ ትምክህትንና ራሱ እግዚአብሔርን የሚቃወም ሰው አይወድም ዘዳግ 5÷ 10 አስመ አነ አምላክ ቀናኢ እኔ እግዚአብሔር ቀናተኛ አምላክ ነኝ ሲል በሙሴ አፍ እንዳስተማረ የሚቃወሙትን የቃወማቸዋል ፡፡ Read more https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/5.3.jpg 480 640 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2013-01-17 07:11:522013-01-17 07:11:52ዓመታዊው የዓጋዓዝተ ዓለም ሥላሴ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ
የልደት በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቅት ተከበረJanuary 7, 2013 በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት ተወልዶላችኋል ሉቃ.2፥11 እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡ የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ታላላቅ በዓላቶች መካከል አንዱ ሲሆን ሁሌ በየዓመቱ ታኅሣሥ 29 እንደሚከበር ይታወቃል፡፡ እንደ ተለመደው የዘንድሮ በዓልም መከበር የጀምረው ከዋዜማው 12.00 ሰዓት ጀምሮ ሲሆን በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማትና አድባራት ሥራዓተ ማኅሌት፤ሰዓታት እና ሥርዓተ ቅዳሴ ሲከናወን ያድራል ፡፡ በተለይም በአገሪቱ ዋና መዲና በሆነቸው በአዲስ አበባ ከተማ በሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በመንበረ ጸባዖት ቅድሰት ሥላሴ ካቴድራል በዓሉ እጅግ በጣም በማቅ ሁኔታ ተከብሮ አድሯል፡፡በበዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፤ ዶ/ር ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ፤ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ፤በፁዕ አቡነ አረጋዊ የመንበረ ጸባዖት ቅድሰት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ኃላፊ ፤ካህናት እና በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ምዕመናን በበዓሉ ላይ ተኝተው በዓሉን በድምቀት አክብረዋል፡፡በዐቃቤ መንበር ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል መልካም ፈቃድ ሥርዓተ ቅዳሴውን የመሩት ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ሲሆኑ በ3ቱም መንበር በሥላሴ፤በማርያምና በዮሐንስ ቤተ መቅደሶች ቅዳሴው የተቀደሰ ሲሆን ሥርዓተ ቅዳሴውም በተለመደው ሰዓት ተጠናቅቋል፡፡ በበዓሉ ላይ ለተገኙ መዕመናን በዐቃቤ መንበር ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል አማካኝነት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ተሰጥቶ የበዓሉ ፍፃሜ ሁኗል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሁሌ በየዓመቱ የሚከበረው የቅዱስ በዓለ ወልድ በዐለ ንግሥ ታኅሣሥ 29/2005 ዓ.ም በድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡ቅዱስ በዓለ ወልድ በአዲስ አበባ ከሚገኙ ታላላቅ ገዳማትና አድባራት መካከል አንዱ ሲሆን የተመሠረተውም በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን መንግስት በ1883ዓም እንደሆነ ይታወቃል፡፡ Read more https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/03.jpg 480 640 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2013-01-07 16:21:062013-01-07 16:21:06የልደት በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቅት ተከበረ
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የገና 2005ዓ.ም በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡January 6, 2013 በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መግለጫ ሲሰጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልእክት “በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ እንዲሁም የሕግ ታሪሚዎች ሆናችሁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት እንኳን ለ2005 ዓ.ም. የጌታችን የአምላካችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዐለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡” ካሉ በኋላ “በጌታችን ቤዛነት እንድን ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮአልና፤ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር በዚህ አውቀናል፡፡ እግዚአብሔር ከፍጡራን ሁሉ የተለየና ከአእምሮ በላይ የሆነ መለኮታዊ ኀይል ያለው አምላክ በመሆኑ የባሕርዩን ጥልቅነት በምልአት ማወቅ ፈጽሞ የማይቻል ቢሆንም እርሱ ራሱ በገለጸልን መጠን የተወሰኑ ነገሮችን እናውቃለን፡፡ Read more https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/abune_nathnael.jpg 718 868 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2013-01-06 12:49:172013-01-06 12:49:17ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የገና 2005ዓ.ም በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡
በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን ለ3ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠJanuary 6, 2013ከአሁን በፊት በዌብሳይታችን አማካኝነት ወጣት ብሩክ አስራት ከዛሬ 3 ወር በፊት ጀምሮ ለካቴድራሉ አረጋውያን የሚሆን በየወሩ ለአረጋውያኑ የሚያስፈልጋቸውን የምግብ እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ስንዘግብ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን አሁንም እንደተለመደው ለ3ኛ ጊዜ ለገና በዓል መዋያ የሚሆን፡- 25 ሌትር ጋዝ፤ 15 ሌትር ዘይት 15 ኪሎ ስኳር፤ 15 ኪሎ በርበሬ፤ 15 ኪሎ ሽሮ፤5 […] Read more https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/holytrinity/02.jpg 480 640 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2013-01-06 12:28:392013-01-06 12:28:39በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን ለ3ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ
የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ልዩ እድሳት እንደሚያስፈልገው ተገለፀ፡፡November 25, 2012 በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሰበካ ጉባኤ አስተዳደር ጽ/ቤት እንደገለፀው የካቴድራሉ ህንፃ ወስጣዊም ሆነ ውጫዊው ክፍሉ ከጊዜ ብዛት የተነሳ የመሰነጣጠቅ ሁኔታ እየታየበት በመምጣቱ አስቸኳይ የሆነ ሙሉ እድሳት እንደሚያስፈልገውና ጥናቱ በጥንቃቄ እንዲጠና ከበላይ አካልም ጭምር ስለታነበት በባለሞያዎች በምን ዓይነት ሁኔታ መታደስ እንዳለበት ከመጋቢት 2ዐዐ4 ዓ.ም ጀምሮ ጥንቃቄ በተሞላበት ሙሉ ጥናት ሲደረግበት ቆይቶ […] Read more https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/img_0044.jpg 480 640 tc https://eotc-htc.org/a/wp-content/uploads/logo_am2.png tc2012-11-25 18:03:472012-11-25 18:03:47የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ልዩ እድሳት እንደሚያስፈልገው ተገለፀ፡፡
ዓመታዊው የዓጋዓዝተ ዓለም ሥላሴ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ
እንኳን ለአብርሃሙ ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና በሕይወት አደረሳችሁ፡፡
በመ/ር ዘሩ እና በመ/ር ዳዊት
‹‹እመ እግዚአብሔር ኢሐነፀ ቤተ ከንቶ ይፃምው እለ የሃንፁ›› ‹‹እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ ግንበኞቹ በከንቱ ይደክማሉ›› መዝ 126፡1 ይህን የታላቁን ነቢይ ቃል ለመነሻነት የተመረጠው ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን የሚከበረው የአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በዓለ ንግሥን ምክንያት ለመግለፅ ነው፡፡ ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ዳዊት ምንም እንኳ ይህን ኃይለ ቃል ከጊዜ በኋላ የፃፈው ቢሆንም የዚህን ጽሑፍ ሐሳብ የሚያንፀባርቀው ቀደም ሲል በዘመነ ህገ ልቡና የተፈፀመ ነበረ በዘፍ1ዐ፡32 ላይ ‹‹የኖኀ የልጆቹ ነገዶች እንደየ ትውልዳቸው በየህዝባቸው እነዚህ ናቸው፤ አህዛብም ከጥፋት ውኃ በኋላ በምድር ላይ ከነዚህ ተከፋፈሉ››፡፡ ይልና በተለይ በዘፍ 11፡1 ጀምሮ ያለውን ስንመለከት ደግሞ ‹‹ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋ ንግግር ነበረች›› ብሎ የሰናኦርን ግንብ መገንባትና መፍረስን ያትታል፡፡ በአጭሩ የዚህ ኃይለ ቃል ጭብጥ ሐሳብ፡- የሰው ልጆች እግዚአብሔርን ለመቃወም ሲሉ ታላቅ ግንብ እንደገነቡና እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ታላቅ ግንብ እንደ አፈራረሰባቸው ነው የሚያብራራው፡፡ ይህን ግንብ ለመገንባት 43 ዓመት ፈጅቶባቸዋል፡፡
ይህ ግንብ በአሁኑ ዘመን በነዱባይ ከተገነቡት ታላላቅ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች እንደሚበልጥ የቤተ ክርስቲያኒቱ መምህራን ይናገራሉ፡፡ ይህንን ህንፃ ሲገነቡ የነበሩ ሰዎች ቀደም ሲል እንደተገለፀው ለትምክህትና እግዚአብሔርን ለመቃወም ስለሆነ እግዚአብሔር ደግሞ ትምክህትንና ራሱ እግዚአብሔርን የሚቃወም ሰው አይወድም ዘዳግ 5÷ 10 አስመ አነ አምላክ ቀናኢ እኔ እግዚአብሔር ቀናተኛ አምላክ ነኝ ሲል በሙሴ አፍ እንዳስተማረ የሚቃወሙትን የቃወማቸዋል ፡፡
የልደት በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቅት ተከበረ
በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ
እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት ተወልዶላችኋል ሉቃ.2፥11
እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡
የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ታላላቅ በዓላቶች መካከል አንዱ ሲሆን ሁሌ በየዓመቱ ታኅሣሥ 29 እንደሚከበር ይታወቃል፡፡ እንደ ተለመደው የዘንድሮ በዓልም መከበር የጀምረው ከዋዜማው 12.00 ሰዓት ጀምሮ ሲሆን በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማትና አድባራት ሥራዓተ ማኅሌት፤ሰዓታት እና ሥርዓተ ቅዳሴ ሲከናወን ያድራል ፡፡ በተለይም በአገሪቱ ዋና መዲና በሆነቸው በአዲስ አበባ ከተማ በሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በመንበረ ጸባዖት ቅድሰት ሥላሴ ካቴድራል በዓሉ እጅግ በጣም በማቅ ሁኔታ ተከብሮ አድሯል፡፡በበዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፤ ዶ/ር ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ፤ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ፤በፁዕ አቡነ አረጋዊ የመንበረ ጸባዖት ቅድሰት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ኃላፊ ፤ካህናት እና በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ምዕመናን በበዓሉ ላይ ተኝተው በዓሉን በድምቀት አክብረዋል፡፡በዐቃቤ መንበር ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል መልካም ፈቃድ ሥርዓተ ቅዳሴውን የመሩት ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ሲሆኑ በ3ቱም መንበር በሥላሴ፤በማርያምና በዮሐንስ ቤተ መቅደሶች ቅዳሴው የተቀደሰ ሲሆን ሥርዓተ ቅዳሴውም በተለመደው ሰዓት ተጠናቅቋል፡፡ በበዓሉ ላይ ለተገኙ መዕመናን በዐቃቤ መንበር ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ናትናኤል አማካኝነት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ተሰጥቶ የበዓሉ ፍፃሜ ሁኗል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሁሌ በየዓመቱ የሚከበረው የቅዱስ በዓለ ወልድ በዐለ ንግሥ ታኅሣሥ 29/2005 ዓ.ም በድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡ቅዱስ በዓለ ወልድ በአዲስ አበባ ከሚገኙ ታላላቅ ገዳማትና አድባራት መካከል አንዱ ሲሆን የተመሠረተውም በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን መንግስት በ1883ዓም እንደሆነ ይታወቃል፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የገና 2005ዓ.ም በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡
በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መግለጫ ሲሰጡ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልእክት “በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ እንዲሁም የሕግ ታሪሚዎች ሆናችሁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት እንኳን ለ2005 ዓ.ም. የጌታችን የአምላካችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዐለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡” ካሉ በኋላ “በጌታችን ቤዛነት እንድን ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮአልና፤ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር በዚህ አውቀናል፡፡ እግዚአብሔር ከፍጡራን ሁሉ የተለየና ከአእምሮ በላይ የሆነ መለኮታዊ ኀይል ያለው አምላክ በመሆኑ የባሕርዩን ጥልቅነት በምልአት ማወቅ ፈጽሞ የማይቻል ቢሆንም እርሱ ራሱ በገለጸልን መጠን የተወሰኑ ነገሮችን እናውቃለን፡፡
በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለሚጦሩ 15 አረጋወያን ለ3ኛ ጊዜ እረዳታ ተሰጠ
ከአሁን በፊት በዌብሳይታችን አማካኝነት ወጣት ብሩክ አስራት ከዛሬ 3 ወር በፊት ጀምሮ ለካቴድራሉ አረጋውያን የሚሆን በየወሩ ለአረጋውያኑ የሚያስፈልጋቸውን የምግብ እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ስንዘግብ መቆየታችን የሚታወስ ሲሆን አሁንም እንደተለመደው ለ3ኛ ጊዜ ለገና በዓል መዋያ የሚሆን፡- 25 ሌትር ጋዝ፤ 15 ሌትር ዘይት 15 ኪሎ ስኳር፤ 15 ኪሎ በርበሬ፤ 15 ኪሎ ሽሮ፤5 […]
የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ልዩ እድሳት እንደሚያስፈልገው ተገለፀ፡፡
በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሰበካ ጉባኤ አስተዳደር ጽ/ቤት እንደገለፀው የካቴድራሉ ህንፃ ወስጣዊም ሆነ ውጫዊው ክፍሉ ከጊዜ ብዛት የተነሳ የመሰነጣጠቅ ሁኔታ እየታየበት በመምጣቱ አስቸኳይ የሆነ ሙሉ እድሳት እንደሚያስፈልገውና ጥናቱ በጥንቃቄ እንዲጠና ከበላይ አካልም ጭምር ስለታነበት በባለሞያዎች በምን ዓይነት ሁኔታ መታደስ እንዳለበት ከመጋቢት 2ዐዐ4 ዓ.ም ጀምሮ ጥንቃቄ በተሞላበት ሙሉ ጥናት ሲደረግበት ቆይቶ […]